ፈልግ

ር.ሊ.ጳ ፍራንችስኮስ በዐብይ ጾም ወቅት የእግዚአብሄርን ድምጽ መስማት ይኖርብናል ማለታቸው ተገለጸ!

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ዘወትር እሁድ እለት በቫቲካን በሚገኘው የቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለሚሰበሰቡ ምዕመናን በእለቱ በሚነበበው የቅዱስ ወንጌል ክፍል ላይ ተንተርሰው አስተንትኖ እንደሚያደርጉ ይታወቃል። በእዚህ መሰረት ቅዱስነታቸው በየካቲት 10/2016 ዓ.ም ባደርጉት አስተንትኖ በእዚህ የዐብይ ጾም ወቅት የእግዚአብሔርን ድምጽ መስማት ይኖርብናል ማለታቸው ተገልጿል።

የእዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

የተወዳችሁ ወንድሞቼ እና እንደምን አረፈዳችሁ!

ዛሬ የዐብይ ጾም በተጀመረበት የመጀመሪያ ሰንበት ላይ የተነበበው ቅዱስ ወንጌል ኢየሱስ በምድረ በዳ የተፈተነበትን ሁኔታ ያቀርብልናል (ማር. 1፡12-15)። የመጽሐፍ ቅዱሱ ታሪክ “በምድረ በዳ በሰይጣን ተፈትኖ አርባ ቀን ኖረ” ይላል። እኛም በዐቢይ ጾም ወቅት “ወደ ምድረ በዳ እንድንገባ” ተጋብዘናል፣ ማለትም፣ ዝምታ፣ ውስጣዊው ዓለም፣ ልብን እንድንሰማ፣ ከእውነት ጋር እንድንገናኝ ተጋብዘናል። የዛሬው ቅዱስ ወንጌል በምድረ በዳ ውስጥ ክርስቶስ “ከአውሬዎች ጋር ነበረ” በማለት ተናግሯል። መላእክትም አገለግሉት” (ማርቆስ 1፡13)። የዱር አራዊት እና መላእክት የእርሱ ማህበርተኞች ነበሩ። ነገር ግን፣ በምሳሌያዊ አነጋገር፣ እነሱ የእኛም አጃቢዎች ናቸው፡ በእርግጥ፣ ወደ ውስጠኛው ምድረ በዳ ስንገባ፣ እዚያ የዱር አራዊትና መላእክትን እናገኛለን።

የዱር አራዊት! በምን መልኩ? በመንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ ልብን የሚከፋፍሉ፣ ውስጣቸውን ለመያዝ የሚሞክሩ እንደ ሥር የሰደዱ ስሜቶች ልንላቸው እንችላለን። እነሱ ያታልሉናል፣ አሳሳች ይመስላሉ፣ ካልተጠነቀቅን ግን እነርሱ ይበጣጥሱናል። ለነዚህ የነፍስ “አውሬዎች” ስም ልንሰጣቸው እንችላለን፡- የተለያዩ ምግባሮች፣ የሀብት መመኘት፣ በመተሳሰብና ባለመርካት ወደ እስር ቤት የሚያስገባን፣ የተድላ ከንቱነት፣ ዕረፍት ማጣትና ብቸኝነት የሚፈርጅ፣ ዝናን የመሻት ፍላጎት። አለመተማመንን እና ቀጣይነት ያለው የማረጋገጫ እና ታዋቂነት ፍላጎት የሚፈጥር - በውስጣችን ሊያጋጥሙን የሚችሉትን እነዚህን ነገሮች መዘንጋት የለብንም - ስግብግብነት ፣ ከንቱነት እና ራስ ወዳድነት። እንደ “ዱር” አውሬዎች ናቸው፣ እና እንደዚሁ መቃወም እና መታገል አለብን። ያለበለዚያ ነፃነታችንን አግበስብሰው ይወስዳሉ። እናም እነዚህን ነገሮች ለማስተካከል ወደ ውስጠኛው ምድረ በዳ እንድንገባ ይርዳን።

ከዚያም በምድረ በዳ መላእክት ነበሩ። እነዚህ የእግዚአብሔር መልእክተኞች ናቸው፣ የሚረዱን፣ በጎ የሚያደርጉልን ናቸው፡ በእርግጥም ባህሪያቸው፣ በወንጌል መሰረት፣ አገልግሎት ነው (ማርቆስ 1፡13)፣ ሀብት ከማካበት ጋር ፍፁም ተቃራኒ፣ የስሜታዊነት ዓይነተኛ ምልክቶች ናቸው። ሀብት ከማጋበስ በተቃራኒ የሚደረግ አገልግሎት። የመላእክት መንፈስ ይልቁንም በመንፈስ ቅዱስ የተጠቆሙትን መልካም ሀሳቦች እና ስሜቶች ያስታውሳሉ። ፈተናዎች ሲለያዩን፣ መልካም ነገሮች መለኮታዊ መነሳሻዎች አንድ ያደርጉናል እና ወደ ስምምነት እንግባ፡ ልብን ያረካሉ፣ የክርስቶስን ጣዕም፣ “የገነትን ጣዕም” ያጎናጽፋሉ። እናም የእግዚአብሔርን መነሳሳት ለመረዳት አንድ ሰው ወደ ጸጥታ እና ጸሎት መግባት አለበት። የዐብይ ጾም ጊዜ ደግሞ ይህን ለማድረግ ነው የሚጠቅመን።

ራሳችንን ልንጠይቅ እንችላለን፣ በመጀመሪያ፣ በልቤ ውስጥ የሚቀሰቅሱት የተዘበራረቁ ስሜቶች፣ “አውሬዎች” ምንድን ናቸው? ሁለተኛ ጥያቄ፡ የእግዚአብሔር ድምፅ ለልቤ እንዲናገር እና በመልካምነት እንዲጠብቀው ለመፍቀድ፣ ወደ “ምድረ በዳ” ትንሽ ለማፈግፈግ እያሰብኩ ነው፣ በዚህ ቀን ቦታን ለመስጠት እየሞከርኩ ነው?

ቃሉን የጠበቀች ለክፉው ፈተና እራሷን ያላስደፈረችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዐብይ ጾም ጉዟችን መልካም ነገር እንድናደርግ እርሷ ትርዳን።

19 February 2024, 09:24

የገብርኤል ብሥራት ጥንታዊ መሠርት የያዘና የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ሰው መሆን በማስታወስ በቀን ሦስት ጊዜ ማለትም በንጋት (በአስራሁለት ሰዓት) በቀትር (በስድስት ሰዓት) እንዲሁም በማታ (በአስራሁለት ሰዓት) የሚደገም የጸሎት ዓይነት ሲሆን ጸሎቱ በሚደገምበት ሰዓት ቤተ ክርስቲያንም የመልኣከ እግዚኣብሔርን ደወል በዚሁ ሰዓት ትደውላለች። ይህ ጸሎት መልኣከ እግዚኣብሔር የሚለውን ስያሜ ያገኝው ከጸሎቱ ከመጀመሪያ ስንኝ የእግዚኣብሔር መልኣከ ማርያምን አበሠራት ከሚለው የተወሰደ ሲሆን ጸሎቱ ስለ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን ይናገራል። ጸሎቱ በሦስት የተከፈሉ አጫጭር ስንኞች ሲኖሩት በእነኚህ በሦስት አጫጭር ስንኞች መሓል ጸጋን የተሞላሽ የሚለው የማርያም ጸሎት ይደገማል። ይህ ጸሎት በሰንበትና በበዓላት ዕለት ልክ በእኩለ ቀን ላይ በዕለቱ ወንጌል ላይ ትንሽ አስተምሮና ገለፃ ከሰጡ በኋላ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በቅዱስ ጴጥሮስ ኣደባባይ ላይ ይህንን ጸሎት ይመራሉ። በመቀጠልም በአደባባዩ ላይ የተገኝው ከተለያየ ቦታ ለንግደት የመጣውን ሕዝብ ሰላምታ ይሰጣሉ።በየትኛውም ጊዜ ከበዓለ ፋሲካ እስከ በዓለ ጰራቅሊጦስ በመልኣከ እግዚኣብሔር ጸሎት ፈንታ የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ የሚዘክረውን “የሰማይ ንግሥት ሆይ ደስ ይበልሽ” የሚለው ጸሎት የሚደገም ሲሆን በመሓል በመሓሉ ጸጋን የተሞላሽ ማርያም ሆይ የሚለው ጸሎት ይታከልበታል።

መልኣኩ ገብርኤል ማሪያምን አበሰራት የሚለው የቀርብ ጊዜ ጸሎት

ሁሉንም ያንብቡ >