ፈልግ

ር.ሊ.ጳ ፍራንችስኮስ በእነዚህ የስብከተ ገና ሳምንታት ውስጥ የሌሎችን ችግር መመልከት ይኖርባናል አሉ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ዘወትር እሁድ በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለሚሰበሰቡ ምዕመናን እና የሀገር ጎብኚዎች በእለቱ ቅዱስ ወንጌል ላይ ተንተርሰው አስተንትኖ እንደምያደርጉ ይታወቃል። በእዚህ መሰረት ባለፈው እሁድ ኅዳር 23/2016 ዓ.ም የጎርጎሮሳዊያኑን የቀን አቆጣጠር በሚከተሉ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ምዕመናን ዘንድ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል ዝግጅት ይሆን ዘንድ በተጀመረው የአንደኛ የስብከተ ገና ሳምንት ላይ ቅዱስነታቸው በሁኑ ወቅት በገጠማቸው የጤና እክል ምክንያት አስተንትኖውን ያደረጉት በቫቲካን ውስጥ ከሚገኘው የቅድስት ሀና የጸሎት ቤት ውስጥ ሆነው እንደ ነበረ የተገለጸ ሲሆን በእነዚህ የስብከተ ወንጌል ሳምንታት ውስጥ ለራሳችን ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም መኖር ይገባናል ማለታቸው ተገልጿል።

የእዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ በወቅቱ ያደረጉትን የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ ሙሉ ይዘቱን እንደሚከተለው አሰናድተነዋል፣ ተከታተሉን።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንደምን አረፈዳችሁ!

ዛሬ ደግሞ ሁሉንም ነገር ማንበብ አልችልም፣ እየተሻለኝ ነው፣ ነገር ግን ድምፄ አሁንም ጥሩ አይደለም። የእኔታ አባ ብሬዳ የቅዱስ ወንጌሉን አስተንትኖ በእኔ ስም ሆነው ያነቡላችኋል።

ዛሬ በመጀመሪያው የስብከተ ገና ሳምንት መጀመሪያ እለተ ሰንበት ስርዓተ አምልኮ ላይ የተነበበው ቅዱስ ወንጌል  (ማር. 13፡33-37) ውስጥ ኢየሱስ ሦስት ጊዜ ቀላል እና ቀጥተኛ የሆነ ምክር ለእኛ በመስጠት ሦስት ጊዜ “ተመልከቱ” (ማርቆስ 13፡ 33፣ 35፣ 37) ይለናል።

ስለዚህ ጭብጡ መንቃት የሚለው ቃል ይሆናል ማለት ነው። እንዴት ልንረዳው ይገባል? አንዳንድ ጊዜ ይህን ፀጋ ጥፋትን በመፍራት የተነሳሳ አመለካከት አድርገን እናስባለን፤ ትልቅ የሆነ ድንጋይ ከሰማይ  ለመውደቅ እንደሚዝት፣ በጊዜው ካላስወገድነው፣ እኛን ሊያጨናንቀን ይችላል። ነገር ግን ይህ በእርግጠኝነት ክርስቲያናዊ ንቃት ማለት አይደለም!

ኢየሱስ ይህንን በምሳሌ አስረድቶታል፣ ከሄደበት ስለሚመለስ ጌታ እና እርሱን ስለሚጠባበቁት አገልጋዮቹ ተናግሯል (ማርቆስ 13. 34)። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያለው አገልጋይ ብዙውን ጊዜ የትብብር እና የፍቅር ግንኙነት ያለው የጌታው "የታመነ ሰው" ነው። ለምሳሌ ሙሴ የእግዚአብሔር አገልጋይ ተብሎ መገለጹን አስቡ (ዘኁ. 12፡7)፣ እና ማርያም እንኳን ስለ ራሷ፣ “እነሆ፣ እኔ የጌታ ባሪያ ነኝ” (ሉቃስ 1፡38) ብላለች። ስለዚህ የአገልጋዮቹ ንቃት የፍርሃት ሳይሆን የመናፈቅ፣ የሚመጣውን ጌታቸውን ለመገናኘት መውጣትን መጠበቅ ነው። እርሱን ስለሚንከባከቡት ለመምጣቱ ዝግጁ ሆነው ይቆያሉ፣ ምክንያቱም ተመልሶ በሚመጣበት ጊዜ እንግዳ ተቀባይና ሥርዓት ያለው ቤት ውስጥ እንደሚቀበሉት   ስላሰቡ ነው። እርሱን በማየታቸው ደስተኞች ናቸው፣ ይህም እነርሱ አካል ለሆኑበት ለመላው ታላቅ ቤተሰብ በዓል ሆኖ ተመልሶ እንዲመጣ በጉጉት ይጠባበቃሉ።

ኢየሱስን ለመቀበል እራሳችንን ማዘጋጀት የምንፈልገው በፍቅር የተሞላው በዚህ ተስፋ ነው፡ በገና ከጥቂት ሳምንታት በኋላ በምናከብረው በዓል ላይ ማለት ነው። በዘመኑ ፍጻሜ ላይ በክብር ሲመለስ; በየቀኑ፣ በቅዱስ ቁርባን፣ በቃሉ፣ በወንድሞቻችን እና በእህቶቻችን፣ በተለይም በጣም በተቸገሩት ሰዎች ውስጥ ሆኖ ሊገናኘን የመጣል።

ስለዚህ በእነዚህ ሳምንታት ውስጥ በልዩ ሁኔታ የልባችንን ቤት በሥርዓት እና እንግዳ ተቀባይ እንዲሆን በጥንቃቄ እናዘጋጅ። እንዲያውም ነቅቶ መጠበቅ ማለት ልብን ዝግጁ ማድረግ ማለት ነው። በሌሊት በድካም የማይፈተነው፣ እንቅልፍ የማይወስደው፣ የሚመጣውን ብርሃን እየጠበቀ ነቅቶ የሚኖረው የልኡካን አመለካከት ነው። ጌታ ብርሃናችን ነው እና በጸሎት መንፈስ እንዲቀበለው እና በበጎ አድራጎት ምግባር ልናስተናግደው ልባችንን ማዘጋጀቱ መልካም ነው፣ ማለት ሁለቱ ዝግጅቶች ለመናገር ምቾት እንዲሰማቸው ያደርጋል። በዚህ ረገድ የጸሎት ሰው የሆነው ቅዱስ ማርቲን ቱርስ፣ ካባውን ግማሹን ለአንድ ድሀ ከሰጠ በኋላ፣ ኢየሱስ የሰጠውን ካባ ለብሶ ሲያየው እንደነበረ ታሪኩ ይናገራል። ለስብከተ ገና የሚሆን ጥሩ ዝግጅት ይኸውና፡ ኢየሱስን ወደ ሚፈልጉን ወንድሞች እና እህቶች ሁሉ ሲመጣ ለመገናኘት እና የምንችለውን ከእነሱ ጋር ለመካፈል ለማዳመጥ ጊዜ እና ተጨባጭ እገዛ ያስፈልጋል።

ውድ ጓደኞቼ፣ ለጌታ እንዴት ደስ የሚል ልብ ማዘጋጀት እንደምንችል ራሳችንን መጠየቃችን ይጠቅመናል። ወደ ይቅርታው፣ ወደ ቃሉ፣ ወደ መንበረ ታቦቱ በመቅረብ፣ ለጸሎት ቦታ በመስጠት፣ የተቸገሩትን በመቀበል ልናደርገው እንችላለን። እራሳችንን በብዙ ትርጉም በሌላቸው ነገሮች ሳናማርር፣ እና ሁል ጊዜ ሳንበሳጭ ነገር ግን ልባችንን ነቅተን፣ ማለትም ለእርሱ በመጓጓት፣ ነቅተን እና ዝግጁ፣ እርሱን ለመገናኘት ትዕግስት በማጣት በጉጉት እርሱን  የእርሱን የመጠባበቅ መንፈስ ልናዳብር ይገባል።

በተስፋ የምትጠባበቁት ድንግል ማርያም የሚመጣውን ልጇን እንድንቀበል እርሷ በአማልጅነቷ ትርዳን።

04 December 2023, 09:41

የገብርኤል ብሥራት ጥንታዊ መሠርት የያዘና የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ሰው መሆን በማስታወስ በቀን ሦስት ጊዜ ማለትም በንጋት (በአስራሁለት ሰዓት) በቀትር (በስድስት ሰዓት) እንዲሁም በማታ (በአስራሁለት ሰዓት) የሚደገም የጸሎት ዓይነት ሲሆን ጸሎቱ በሚደገምበት ሰዓት ቤተ ክርስቲያንም የመልኣከ እግዚኣብሔርን ደወል በዚሁ ሰዓት ትደውላለች። ይህ ጸሎት መልኣከ እግዚኣብሔር የሚለውን ስያሜ ያገኝው ከጸሎቱ ከመጀመሪያ ስንኝ የእግዚኣብሔር መልኣከ ማርያምን አበሠራት ከሚለው የተወሰደ ሲሆን ጸሎቱ ስለ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን ይናገራል። ጸሎቱ በሦስት የተከፈሉ አጫጭር ስንኞች ሲኖሩት በእነኚህ በሦስት አጫጭር ስንኞች መሓል ጸጋን የተሞላሽ የሚለው የማርያም ጸሎት ይደገማል። ይህ ጸሎት በሰንበትና በበዓላት ዕለት ልክ በእኩለ ቀን ላይ በዕለቱ ወንጌል ላይ ትንሽ አስተምሮና ገለፃ ከሰጡ በኋላ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በቅዱስ ጴጥሮስ ኣደባባይ ላይ ይህንን ጸሎት ይመራሉ። በመቀጠልም በአደባባዩ ላይ የተገኝው ከተለያየ ቦታ ለንግደት የመጣውን ሕዝብ ሰላምታ ይሰጣሉ።በየትኛውም ጊዜ ከበዓለ ፋሲካ እስከ በዓለ ጰራቅሊጦስ በመልኣከ እግዚኣብሔር ጸሎት ፈንታ የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ የሚዘክረውን “የሰማይ ንግሥት ሆይ ደስ ይበልሽ” የሚለው ጸሎት የሚደገም ሲሆን በመሓል በመሓሉ ጸጋን የተሞላሽ ማርያም ሆይ የሚለው ጸሎት ይታከልበታል።

መልኣኩ ገብርኤል ማሪያምን አበሰራት የሚለው የቀርብ ጊዜ ጸሎት

ሁሉንም ያንብቡ >