ፈልግ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ ኢየሱስ በዕርገቱ ወደ ሰማይ መንገድ ይመራናል አሉ።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ዘወትር እሁድ እለት በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለሚሰበሰቡ ምዕመናን በእለቱ በሚነበበው የቅዱስ ወንጌል ክፍል ላይ ተንተርሰው አስተንትኖ እንደሚያደርጉ የሚታወቅ ሲሆን በእዚህ መሰረት ቅዱስነታቸው በግንቦት 13/2015 ዓ.ም ባደረጉት አስተንትኖ ኢየሱስ በዕርገቱ ወደ ሰማይ መንገድ ይመራናል ማለታቸው ተገልጿል።

የእዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ በወቅቱ ያደረጉትን አስተንትኖ ሙሉ ይዘቱን እንደሚከተለው አሰናድተነዋል፣ ተከታተሉን።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንደምን አረፈዳችሁ!

ዛሬ በጣሊያን እና በሌሎች በርካታ አገሮች የጌታ ዕርገት በዓል እየተከበረ ይገኛል። እኛ ሁላችን በደንብ የምናውቀው በዓል ነው ፣ ነገር ግን ብዙ ጥያቄዎችን ሊያመጣ ይችላል - ቢያንስ ሁለት። የመጀመሪያው የኢየሱስን ከምድር ተለይቶ ወደ ሰማይ መውጣቱን የምናከብረው ለምንድን ነው? የሱ ወደ ሰማይ መውጣት የሚያሳዝን እንጂ የሚያስደስት ነገር አይመስልም! ሁለተኛው ጥያቄ፡- ኢየሱስ አሁን በሰማይ ምን እያደረገ ነው… እዚያ መገኘቱ አስፈላጊ የሆነው ለምንድነው? ለምን እያከበርን ነው እና ኢየሱስ አሁን ምን እያደረገ ነው፡ እነዚህ ሁለት ጥያቄዎች ናቸው የምናከብረውን በዓል በሚገባ እንድንረዳ የሚያደርጉን።

የሰው ልጅ በሰማይ

ለምን እያከበርን ነው። ምክንያቱም ከእርገቱ ጋር አንድ አዲስ እና የሚያምር ነገር ተከስቷል፡ ኢየሱስ ሰባዊነታችንን ወደ ሰማይ ማለትም ወደ እግዚአብሔር እንዲወጣ አድርጓል። ያ በምድር ላይ ያሰበው የሰው ልጅ እዚህ አልቀረም። ወደ እግዚአብሔር ዐረገ በዚያም ለዘላለም ይኖራል። ከዕርገቱ ቀን ጀምሮ፣ እግዚአብሔር ራሱ፣ “ተቀየረ” ማለት እንችላለን – ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እርሱ መንፈስ ብቻ ሳይሆን፣ የራሳችንን ሥጋ፣ ሰውነታችንን የሚሸከም ለእኛ ያለው ፍቅር እንዲህ መሆኑን አሳይቷል! የሚጠብቀን ቦታ በዚህ መንገድ ተጠቁሟል፣ እጣ ፈንታችን ይህ ነው። ስለዚህ አንድ የእምነት ጥንታዊ አባት “እንዴት ያለ አስደሳች ዜና ነው! እኛን ወንድሞቹ ሊያደርገን ስለ እኛ ሰው የሆነው እርሱ ከእርሱ ጋር አብረው ያሉትን ሁሉ ከራሱ ጋር ሊሸከም በአብ ፊት እንደ ሰው አቀረበ። ዛሬ "የሰማይን ድል" እናከብራለን፣ ዛሬ በታላቅ ደስታ ሁል ጊዜ እንደምንለው “ሰማይን በገዛ ጣታችን መንካት” ብቻ ሳይሆን ከሥጋችን ሁሉ ጋር መንካት ችለናል። መንግሥተ ሰማያት ሩቅ አይደለም፣ ቤታችን ነው፣ ኢየሱስ ለእኛ ለማዘጋጀት የሄደበት ቦታ ነው። በአብ ልጆች ሆነን በገነት ለዘላለም እንድንኖር መንገዱን ከፍቶልን እሱን መከተል እንችላለን።

ሁሌም ከኛ ጋር ነው

ሁለተኛው ጥያቄ፡- ኢየሱስ በሰማይ ምን እየሰራ ይገኛል? የሚለው ነው። እርሱ በአብ ፊት ለእኛ አለ፣ ያለማቋረጥ ሰብአዊነታችንን ለእርሱ ያሳያል - ለእኛ ሲል የተቀበለውን ቁስሎች ለእርሱ ያሳያል። እሱ “ይሰራል”፣ ማለትም በአብ ፊት ጠበቃችን ሆኖ (1ዮሐ. 2፡1) ይሠራል። ስለዚህ ብቻችንን አልተወንም። እንዲያውም ከማረጉ በፊት የዛሬ ቅዱስ ወንጌል እንደሚለው “እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ” (ማቴ 28፡20) ብሎ ነግሯል። እርሱ ሁል ጊዜ ከእኛ ጋር ነው፣ እናም ስለ እኛ "ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራል" (ዕብ 7፡25)። በአንድ ቃል ስለዚህ ያማልዳል ማለት እንችላለን። እርሱ ስለ እኛ ሊማልድ በአባቱ እና በእኛ ፊት በተሻለ “ቦታ” አለ። ስለዚህ እኛን ከሁኔታዎች፣ ከችግሮች፣ ከሰዎች እና ከመከራዎቻችን እና ከኃጢአቶቻችን ጋር እንድናቀርብ እየጠበቀን ነው፣ ስለዚህም ለእኛ ይቅርታን እና ምህረትን እንዲያስገኝልን፣ እናም በእሱ እና በአብ ፍቅር ላይ - መንፈስ ቅዱስን እንዲያፈስልን መጠየቅ ይኖርብናል።

ምልጃ መሰረታዊ ነገር ነው። ስለዚህ በዛሬው ቅዱስ ወንጌል ውስጥ፣ ኢየሱስ እንድንጠመድ፣ ወደ ሥራ እንድንገባ፣ “በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እንድንጠመቅ” ጠይቆናል (ማቴ. 28፡19)። ቃል በቃል መጠመቅ ማለት ነው። መጠመቅ ከምስጢራዊ ትርጉሙ በተጨማሪ፣ ሁሉንም ነገር በእግዚአብሔር ውስጥ “ለመዝፈቅ” በተጠራንበት መንገድ ልናስበው እንችላለን - ያጋጠመንን እና የምናገኘውን ሁሉ ማለት ነው። ስለዚህ እራሳችንን እንጠይቅ፡ ይህንን ጥያቄ ራሳችንን እንጠይቅ-እማልዳለሁ ወይ? የማውቃቸውን ሰዎች፣ ችግሮቻቸውን የሚናገሩልኝን፣ በአስቸጋሪ ጊዜያት ውስጥ ያሉትን በእግዚአብሔር ውስጥ “እንዲዘፈቅ” አደርጋለሁ ወይ?” ጸሎቴን ከሚጠብቀው ለኢየሱስ ራሴን አማላጅ አደርጋለውን? መንፈሱን ለእኔ ለሚያቀርብልኝ ለእርሱ ለጌታ ችግሬን አቀርባለሁ ወይ? የቤተክርስቲያን እና የአለምንም ጭምር ችግሮች ለጌታ አቀርባለሁ ወይ? የሰማይ ንግሥት በጸሎት ኃይል እንድናማልድ ትርዳን።

21 May 2023, 09:31

What is the Regina Coeli?

The antiphon Regina Coeli (“Queen of Heaven”) is one of four traditional Marian antiphons, the others being Alma Redemptoris Mater, Ave Regina Coelorum, and Salve Regina.

It was Pope Benedict XIV who, in 1742, enjoined the recitation of the Regina Coeli in place of the Angelus during Eastertide, that is, from Easter Sunday to the end of Pentecost. It is recited standing as a sign of Christ’s victory over death.

Like the Angelus, the Regina Coeli is said three times a day, at dawn, at noon, and at dusk, in order to consecrate the day to God and the Virgin Mary.

This ancient antiphon arose, according to a pious tradition, in the 6th century; it is attested in documentary sources from the first half of the 13th century, when it was inserted in the Franciscan breviary. It is composed of four short verses, each ending with an “alleluia.” With the Regina Coeli, the faithful turn to Mary, the Queen of Heaven, to rejoice with her at the Resurrection of Christ.

At the Regina Coeli on Easter Monday of 2015, Pope Francis spoke about the spiritual dispositions that should animate the faithful as they recite this Marian prayer:

“In this prayer, expressed by the Alleluia, we turn to Mary inviting her to rejoice, because the One whom she carried in her womb is Risen as He promised, and we entrust ourselves to her intercession. In fact, our joy is a reflection of Mary’s joy, for it is she who guarded and guards with faith the events of Jesus. Let us therefore recite this prayer with the emotion of children who are happy because their mother is happy.”

መልኣኩ ገብርኤል ማሪያምን አበሰራት የሚለው የቀርብ ጊዜ ጸሎት

ሁሉንም ያንብቡ >