ፈልግ

BRITAIN-UKRAINE-RUSSIA-ANNIVERSARY-WAR

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በዩክሬን ፍትሃዊ እና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ተማጸኑ!

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ በዩክሬን መጠነ ሰፊ ጦርነት የጀመረበትን ሁለተኛ ዓመት በማስታወስ “ፍትሃዊ እና ዘላቂ ሰላም” ላይ ያተኮረ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ እንዲሰጥ ተማጽነዋል።

የእዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ባለፉት ሁለት ዓመታት ሩሲያ በዩክሬን ላይ ሙሉ ወረራ ከጀመረች በኋላ በደረሰው ሞት፣ ጉዳት፣ ውድመት፣ ጭንቀት እና እንባ አዝነዋል - “ይህ በጣም ረጅም እየሆነ ነው እናም ፍጻሜው ገና ያልታየ ነው” ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ የእሁድ የካቲት 17/2016 ዓ.ም የመላአከ እግዚአብሔር ጸሎት በቫቲካን ካደረጉ በኋላ ባስተላለፉት ሳምንታዊ መልእክት በዩክሬን ያለው ጦርነት “የአውሮፓን አካባቢ እያወደመ ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፍ የፍርሃትና የጥላቻ ማዕበል እየፈጠረ ነው” ሲሉ አስጠንቅቀዋል። 

ቅዱስ አባታችን “ለተሰቃዩት የዩክሬን ሕዝብ” የተሰማቸውን “ከፍተኛ የሆነ ሀዘናቸውን በመግለጽ” እና ጸሎታቸውን ሲያድሱ “ፍትህን ፍለጋ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሔ ለመፍጠር ሁኔታዎችን የሚፈቅድ ያንን ጦርነት የሰው ልጅ እንዲያቆም ተማጽነዋል። ዘላቂ ሰላም ይመጣ ዘንድ ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ጥረት እንዲያደርጉ” ተማጽነዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ በተጨማሪም ሰዎች ለፍልስጤም እና ለእስራኤል እንዲሁም በጦርነቱ ለተበተኑት ብዙ ሰዎች መጸለይን እንዳይዘነጉ አሳስበዋል፣ ለተሰቃዩት በተለይም "ለቆሰሉት፣ ንጹሃን ህጻናት" ተጨባጭ እርዳታ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

በአፍሪካ ውስጥ ግጭቶች

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ብጥብጥ እየጨመረ መሄዱን ገልጸው፣ ከዚች አገር ጳጳሳት ጋር በመሆን የሰላም ጸሎት ጥሪያቸውን በማቅረባቸው ግጭቱ እንዲቆምና “ቅንነትና ገንቢ ውይይት” እንደሚደረግ ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል።

ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ሃሳባቸውን ወደ ናይጄሪያ በማዞር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን አፈና “የሚያሳስብ” ነው ሲሉ አጉልተው የተናገሩ ሲሆን ለናይጄሪያ ህዝብ ያላቸውን ቅርበት እና ጸሎት ገልጿል እናም “የእነዚህን የጥቃት ክፍሎች ስርጭት በተቻለ መጠን ለመግታት ጥረት ይደረጋል” የሚል ተስፋ እንዳላቸው ቅዱስነታቸው ገልጿል።  

የአየር ንብረት ለውጥ፡ አለም አቀፍ ማህበራዊ ችግር

ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሀዘናቸውን ወደ እስያ በማዞር በከባድ ጉንፋን እየተሰቃዩ ካሉት የሞንጎሊያውያን ሕዝብ ጋር ያላቸውን ቅርበት ገልጸው፣ የከፋ ሰብአዊ መዘዝ ከመከሰቱ በፊት ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንዲደረግ ተማጸነዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ "ይህ አስከፊ ክስተት የአየር ንብረት ለውጥ እና የሚያስከትለው ውጤት ምልክት ነው" ብለዋል። “የአየር ንብረት ቀውሱ የብዙ ወንድሞችና እህቶችን ሕይወት በእጅጉ የሚጎዳው ዓለም አቀፋዊ ማኅበራዊ ችግር ነው” ሲል የተናገሩት ቅዱስነታቸው “ፍጥረትን ለመንከባከብ አስተዋጽዖ ለማድረግ ጥበብ የተሞላበትና ደፋር ምርጫዎችን እንድናደርግ እንጸልይ” በማለት ከተናገሩ በኋላ ቅዱስነታቸው መልእክታቸውን አጠናቀዋል።

26 February 2024, 11:21