ፈልግ

ር.ሊ.ጳ ፍራንችስኮስ የኢየሱስን ምሳሌ ተከትለን መልካም ነገሮችን ከመዝራት መታከት የለብንም ማለታቸው ተገለጸ!

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ ዘወትር እሁድ እለት በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለሚሰበሰቡ ምዕመናን በእለቱ በምነበበው የቅዱስ ወንጌል ክፍል ላይ ተንተርሰው የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ እንደምያደርጉ የሚታወቅ ሲሆን በእዚህ መሰረት ቅዱስነታቸው በሐምሌ 9/2015 ዓ.ም ባደረጉት አስተንትኖ የኢየሱስን ምሳሌ ተከትለን መልካም ነገሮችን ከመዝራት መታከት የለብንም ማለታቸው ተገልጿል።

የእዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ በወቅቱ ያደረጉትን የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ ሙሉ ይዘቱን እንደሚከተው አሰናድተነዋል፤ ተከታተሉን።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንደምን አረፈዳችሁ!

የዛሬው ቅዱስ ወንጌል  የዘሪውን ምሳሌ ያቀርብልናል (ማቴ. 13፡1-23)። “መዝራት” በጣም የሚያምር ምስል ሲሆን ኢየሱስ የቃሉን ስጦታ ለመግለጽ ተጠቅሞበታል። አንድን ዘር በዓይነ ሕሊናችን እናስብ፡ ዘሩ ትንሽ ነው፣ ብዙም አይታይም፣ ነገር ግን ፍሬ የሚያፈሩ ተክሎችን ያበቅላል። የእግዚአብሔር ቃል እንደዚህ ነው፡ ወንጌልን አስቡ፣ ቀላል እና ሁሉም ሊደርስበት የሚችል፣ በተቀበሉት ውስጥ አዲስ ሕይወትን የሚሰጥ ነው። ስለዚህ ቃሉ ዘሩ ከሆነ እኛ አፈር ነን፡ መቀበልም ወይም አለመቀበል የራሳችን እጣ ፈንታ ነው። ኢየሱስ ግን “መልካሙ ዘሪ” በልግስና ለመዝራት አይታክትም። መሬታችንን ያውቃል፣ በልባችን ውስጥ ያለውን እንድንለወጥ የማያደርገንን ድንጋዮች እና የጥፋታችን እሾህ (ማቴ 13፡ 21-22) ቃሉን እንደሚያፍን ያውቃል፣ ነገር ግን ተስፋ ያደርጋል፣ የተትረፈረፈ ፍሬ እንድናፈራ ሁልጊዜ ተስፋ ያደርጋል (ማቴዎስ 13፡8)።

ጌታ የሚያደርገው ይህንን ነው እኛ ደግሞ ልናደርገው የሚገባን ይህ ነው፡ ያለመታከት መዝራት። ነገር ግን አንድ ሰው ይህን እንዴት ማድረግ ይችላል፣ ያለማቋረጥ ያለ ድካም ሊዘራ ይችላል? እስቲ ጥቂት ምሳሌዎችን እንውሰድ።

በመጀመሪያ ወላጆች፣ በመጀመሪያ ወላጆች፡ በልጆቻቸው ላይ በጎነትን እና እምነትን ይዘራሉ፣ እናም አንዳንድ ጊዜ ትምህርቶቻቸውን ያልተረዱ ወይም ያልተገነዘቡ ቢመስሉም ወይም የዓለም አስተሳሰብ በእነርሱ ላይ ቢወድቅ ተስፋ ሳይቆርጡ እንዲያደርጉ ተጠርተዋል። ጥሩው ዘር በውስጣቸው ይቀራል፣ ይህ ነው የሚቆጠረው እናም በጊዜው ስር ይሰዳል። ነገር ግን አለመተማመንን ሰጥተው መዝራትን ትተው ልጆቻቸውን በፋሽንና በሞባይል ምህረት ከተዋቸው፣ ጊዜ ሳይሰጡ፣ ሳያስተምሩ፣ ያኔ ለም አፈር በአረም ይሞላል። ወላጆች በልጆቻችሁ ውስጥ ዘር ለመዝራት አትታክቱ!

እንግዲያው ወጣቶችን እንመልከታቸው፡ እነሱም በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ ወንጌልን መዝራት ይችላሉ። ለምሳሌ በጸሎት፡- አንተ ማየት የማትችለው ትንሽ ዘር ናት ነገር ግን የምትኖረውን ሁሉ ለኢየሱስ አደራ ሰጥተህ እንዲበስል ያደርጋል። ነገር ግን እኔ ደግሞ በጣም ለተቸገሩት ለሌሎች ለመስጠት ጊዜ እያሰብኩ ነው፥ ምናልባት የሚባክን ሊመስል ይችላል፥ ይልቁንም ጊዜው የተቀደሰ ነው፥ ነገር ግን የፍጆታ እና ጊዜያዊ ደስታን በማሳደድ የሚገኘውን እርካታ እንደ ባዶ እጅ መሆኑን አይተነዋል። እናም ስለ ትምህርት አስባለሁ፥ እውነት ነው አድካሚ እና ወዲያውኑ አርኪ አይደለም፥ ልክ እንደ መዝራት፣ ነገር ግን ለሁሉም የተሻለ የወደፊት ህይወት ለመገንባት አስፈላጊ ነው።

ወላጆችን አይተናል ወጣቶችን አይተናል፥ አሁን ደግሞ የወንጌል ዘሪዎችን ብዙ ደጋግ ካህናትን፣ ገዳማዊያን ገዳማዊያትን እና በቅዱስ ወንጌል አዋጅ ላይ የተሰማሩትን የእግዚአብሔርን ቃል ብዙ ጊዜ የሚኖሩ እና የሚሰብኩትን አሁን እንመልከት። ቃሉን ስንሰብክ፣ ምንም ነገር የማይሆን በሚመስልበት ቦታ እንኳን፣ በእውነቱ መንፈስ ቅዱስ በሥራ ላይ እንዳለ፣ እና የእግዚአብሔር መንግሥት ከጥረታችን በላይ እያደገ መምጣቱን ፈጽሞ አንርሳ። ስለዚህ፣ ውድ ወንድሞችና እህቶች፣ በደስታ ቀጥሉ! የእግዚአብሔርን ቃል ዘር በህይወታችን ውስጥ ያስቀመጧቸውን ሰዎች እናስታውስ፡ እያንዳንዳችን “እምነታችን እንዴት እንደጀመረ” እናስብ። ምሳሌዎቻቸውን ካገኘን ከዓመታት በኋላ ይበቅላል ፣ ግን ለእነሱ ምስጋና ይግባው!

ከዚህ ሁሉ አንፃር ራሳችንን ልንጠይቅ እንችላለን፡- መልካምነትን እዘራለሁን ወይ? ለራሴ ለማጨድ ብቻ ነው ወይስ ለሌሎችም ነው የምዘራው? በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ አንዳንድ የወንጌል ዘሮችን እዘራለሁ: ጥናት፣ ሥራ፣ ነፃ ጊዜ በእነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ ወንጌልን እዘራለሁ ወይ? ተስፋ ቆርጬ ነው ወይስ ልክ እንደ ኢየሱስ፣ ፈጣን ውጤት ባላገኝም መዝራቴን እቀጥላለሁ ወይ? ዛሬ እንደ ቀርሜሎስ ቅድስት ድንግል ማርያም የምናከብራት ለጋስ እና ደስ የሚል የምስራች ዘሪዎች እንድንሆን እርሷ በአማላጅነቷ ትርዳን።

16 July 2023, 11:02

የገብርኤል ብሥራት ጥንታዊ መሠርት የያዘና የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ሰው መሆን በማስታወስ በቀን ሦስት ጊዜ ማለትም በንጋት (በአስራሁለት ሰዓት) በቀትር (በስድስት ሰዓት) እንዲሁም በማታ (በአስራሁለት ሰዓት) የሚደገም የጸሎት ዓይነት ሲሆን ጸሎቱ በሚደገምበት ሰዓት ቤተ ክርስቲያንም የመልኣከ እግዚኣብሔርን ደወል በዚሁ ሰዓት ትደውላለች። ይህ ጸሎት መልኣከ እግዚኣብሔር የሚለውን ስያሜ ያገኝው ከጸሎቱ ከመጀመሪያ ስንኝ የእግዚኣብሔር መልኣከ ማርያምን አበሠራት ከሚለው የተወሰደ ሲሆን ጸሎቱ ስለ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆን ይናገራል። ጸሎቱ በሦስት የተከፈሉ አጫጭር ስንኞች ሲኖሩት በእነኚህ በሦስት አጫጭር ስንኞች መሓል ጸጋን የተሞላሽ የሚለው የማርያም ጸሎት ይደገማል። ይህ ጸሎት በሰንበትና በበዓላት ዕለት ልክ በእኩለ ቀን ላይ በዕለቱ ወንጌል ላይ ትንሽ አስተምሮና ገለፃ ከሰጡ በኋላ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በቅዱስ ጴጥሮስ ኣደባባይ ላይ ይህንን ጸሎት ይመራሉ። በመቀጠልም በአደባባዩ ላይ የተገኝው ከተለያየ ቦታ ለንግደት የመጣውን ሕዝብ ሰላምታ ይሰጣሉ።በየትኛውም ጊዜ ከበዓለ ፋሲካ እስከ በዓለ ጰራቅሊጦስ በመልኣከ እግዚኣብሔር ጸሎት ፈንታ የጌታችን እየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ የሚዘክረውን “የሰማይ ንግሥት ሆይ ደስ ይበልሽ” የሚለው ጸሎት የሚደገም ሲሆን በመሓል በመሓሉ ጸጋን የተሞላሽ ማርያም ሆይ የሚለው ጸሎት ይታከልበታል።

መልኣኩ ገብርኤል ማሪያምን አበሰራት የሚለው የቀርብ ጊዜ ጸሎት

ሁሉንም ያንብቡ >