ፈልግ

በካንዳ የሚኖሩ ቀደም የአብሮዢያን ሕዝቦች ምስል በካንዳ የሚኖሩ ቀደም የአብሮዢያን ሕዝቦች ምስል 

ቅድስት መንበር የቀደምት ሕዝቦች ዘር የሆኑ ወጣቶችን እንደ ባህል ጠባቂ አድርጋ ትቆጥራለች ተባለ።

እ.አ.አ በሚያዝያ 16/2024 ዓ.ም በኒውዮርክ በተካሄደው 23ኛው ስብሰባ የተባበሩት መንግስታት የቅድስት መንበር ቋሚ ታዛቢ ሊቀ ጳጳስ ገብርኤሌ ካቺያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የቀደምት አገር ተወላጆች ጉዳዮች ላይ ቋሚ ስብሰባ ላይ በሰጡት መግለጫ፣ የቀደምት ሕዝቦች ተወላጆችን በተለይም ወጣቶችን መደገፍ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

የእዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

በተባበሩት መንግሥታት የቅድስት መንበር ቋሚ ታዛቢ ሊቀ ጳጳስ ካቺያ ሚያዝያ 7/2016 ዓ.ም ማክሰኞ እለት በኒውዮርክ በተካሄደው 23ኛው የመንግሥታቱ ድርጅት የቀደምት ተወላጆች ቋሚ ፎረም ላይ ንግግር አድርገዋል።

በተባበሩት መንግስታት የብሔረሰቦች መብት መግለጫ ዐውደ ርዕይ ውስጥ “የአገሬው ተወላጆች የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብትን ማሳደግ፡ የአገሬው ተወላጆችን ድምፅ ማጉላት” የሚል መሪ ቃል ያነገበ ስብሰባ ነበር።

ሊቀ ጳጳሱ ባለፈው ማክሰኞ በሰጡት መግለጫ፣ ቅድስት መንበር ለቋሚ ኮሚተው በአገር በቀል ጉዳዮች ላይ ላከናወነው ተግባር እውቅና ሰጥታለች። በዚህ ዓመት ቅድሚያ የሚሰጠው ጭብጥ ላይ አንዳንድ አስተያየቶችን መስጠታቸውን ገልጸዋል።

ሊቀ ጳጳሱ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአገሬው ተወላጆች መብቶች መግለጫ (UNDRIP) በመጥቀስ “የአገሬው ቀደምት ተወላጅ ወጣቶች ሚና የአሁንና የወደፊት ባህላቸው ጠባቂ መሆናቸውን” መገንዘቡን አስፈላጊነት ገልጿል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ፍትሃዊ እና ሰብአዊነት የሰፈነበት ዓለም ለመገንባት የአገሬው ቀደምት ተወላጅ ወጣቶች መገለልን፣ ብክነትን እና ድህነትን በመዋጋት ባህላቸውንና ሥር መሰረቶቻቸውን እንዲጠብቁ ማበረታታታቸውን አስረድተዋል።

ወጣቶች እንደ ጠባቂ እና ድልድይ አድርጎ መመልከት

የቫቲካን ዲፕሎማት ቀደምት ሕዝቦች የሀገር በቀል ወጣቶች በባህል መስክ እያበረከቱት ስላለው አስተዋፅኦ የበለጠ ተናግረዋል። "የባህላዊ ተግባሮቻቸውን በመጠበቅ እና በማደስ ላይ በንቃት መሳተፍ እና የራሳቸውን ዕድል በራስ የመወሰን መብታቸው ወሳኝ የሆኑትን የማህበረሰባቸውን ልዩ ልዩ የአኗኗር ዘይቤዎች ለመጠበቅ አስተዋፅኦ ማድረግ ይችላሉ" ብለዋል።

የአገሬው ቀደምት ተወላጆች "በትውልድ መካከል ድልድይ ሆነው ያገለገላሉ፣ በትውልድ መካከል ያለውን ውይይት፣ መግባባት እና ትብብርን በማዳበር በማህበረሰባቸው ውስጥ ሰላም እና አንድነት እንዲሰፈን" ሊያገለግሉ ይችላሉ ሲሉ ሊቀ ጳጳሱ አክለው ገልጸዋል።

በተጨማሪም “የአባቶቻቸውን ምድር፣ የተፈጥሮ ሀብትና የአካባቢ ጥበቃ ሥርዓት፣ የአገሬው ተወላጆች የማንነት ቁልፍ አካል የሆኑትን” በመደገፍ ግንባር ቀደም ናቸው ብለዋል።

የውይይት አስፈላጊነት

ሊቀ ጳጳሱ ከአገሬው ቀደም ተወላጆች ጋር የመወያየትን አስፈላጊነት አበረታተዋል፣ እናም ውይይት እና ማንነት “በጋራ የማይነጣጠሉ” እንዴት እንደሆኑም አብራርተዋል። “ሙሉ በሙሉ የተዘጋ፣ ታሪካዊ፣ የማይለዋወጥ ‘አገር በቀል’ ማንኛውም ዓይነት ውህደት የማይቀበል” ሳይሆን “የመገናኘት ባህል” እንዲያራምዱ አሳስቧል።

የቫቲካን ዲፕሎማት ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ባደረጉት ንግግር “የሕዝቦች ሁሉ ፈጣሪ እና አባት እግዚአብሔር ዛሬ ጠርቶናል እናም ለዓለም አቀፋዊ ወንድማማችነት፣ ነፃነት፣ ፍትህ ሰብዓዊ ጥሪያችንን እንድንኖር እና እንድንመሰክር ይጠራናል ብለዋል። ፣ ውይይት፣ የእርስ በርስ ግጭት ለማስወገድ፣ ፍቅርና ሰላም ለመገንባት፣ እና ጥላቻን፣ ቂምን፣ መለያየትን፣ ሁከትንና ጦርነትን ለማስወገድ ይረድናል” ማለታቸውን ሊቀ ጳጳሱ አስታውሰዋል።

 

18 April 2024, 22:21