ፈልግ

 ር.ሊ.ጳ ፍራንችስኮስ የፕላስቲክ ቀዶ ጥገና ሐኪሞች ጋር በቫቲካን በተገናኙበት ወቅት ር.ሊ.ጳ ፍራንችስኮስ የፕላስቲክ ቀዶ ጥገና ሐኪሞች ጋር በቫቲካን በተገናኙበት ወቅት   (Vatican Media)

ር.ሊ.ጳ ፍራንችስኮስ የፕላስቲክ ቀዶ ጥገና ሐኪሞች እውነተኛ ውበት የእግዚአብሔርን መልክ እንደሚያንጸ አስታውሱ አሉ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ለፕላስቲክ የቀዶ ጥገና ሐኪሞች ቡድን ባደረጉት ንግግር ስለ ውበት እውነተኛ ተፈጥሮ የሚገልጹ ሐሳቦችን አንፀባርቀዋል።

የእዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ባለፈው ሐሙስ ዕለት ግንቦት 15/2016 ዓ.ም  የፕላስቲክ የቀዶ ጥገና ሐኪሞችን ቡድን በቫቲካን ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ርኅራኄ ስላለው አገልግሎት በተለይም የታመሙ ሕፃናትን በመርዳታቸው አመስግነዋል።

ከግንቦት 16 እስከ ግንቦት 17/2016 ዓ.ም “ሳይንስ እና ውበት ሲገናኙ” በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው የኤኤክስፒአይ ስብሰባ ላይ ለመካፈል ለተገኙት ሐኪሞች ነበር ንግግር ያደረጉት። ሰው፣ ሐኪሞችና ክርስቲያኖች እንደመሆናችን መጠን ከአካላዊ ውበት ያለፈ ጥሪ ምላሽ እንደሚሰጡ ገልጿል።

እውነተኛ ውበት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ እንዳሉት ከሆነ ለዓይን ከሚታየው ነገር ይበልጣል ብለዋል።

አክለውም ይህ ውበት “በፋሽን ንግድ እና በውጫዊ ውበት የተነደፉ አዝማሚያዎች ጋር የተያያዘ አይደለም ፣ ነገር ግን ከሰው እውነት ጋር የተቆራኘ ነው ፣ እሱ ልንለውጠው የማንችለው በጣም ቅርብ ከሆነው ማንነቱ ጋር ነው” ብለዋል ።

ቅዱስ አባታችን ከቅዱስ ጳውሎስ አስተምህሮ በመነሳት ፊታችን የጌታን ክብር ለማንፀባረቅ፣ በድርጊታችን እና በፍቅራችን ወደ እርሱ መልክ እየለወጠን ነው። የቀዶ ጥገና ሃኪሞቹ ይህ ጥልቅ እውነት እጆቻቸውን እንዲመራቸው አሳስቧቸዋል፣ ይህም ስራቸው በአካል ብቻ ሳይሆን በሁሉም ሰው ላይ የታተመውን የእግዚአብሔርን መልክ የሚያንፀባርቅ እና የሚገልጽ መሆኑን በማረጋገጥ ነው ብለዋል።

በአንድ በኩል፣ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ በመቀጠል፣ ኢየሱስ “በሰው ልጆች መካከል እጅግ ያማረ” ተብሎ ተገልጿል (መዝ 45፡3)። በሌላ በኩል፣ ከመከራው የተነሣ፣ “በሰው ምሳሌ የተበላሸ” ሆኖ ተሥሏል (ኢሳ 52፡14)።

“ኢየሱስ በዚህ ተጻራሪ አባባል (ፓራዶክስ) ያሳየናል፣ በመስቀሉ መንገድ በኩል የሚያልፈውን፣ ታናሽ መሆናችንን በመቀበል፣ ወደ ዘላለማዊ ክብር ለመድረስ፣ የማያሳፍር ወይም የማይመነምን ተስፋ ያስፈልገናል ብለዋል (1ኛ ቆሮ 9፡25)።

 

24 May 2024, 14:40