ፈልግ

ር.ሊ.ጳ. ፍራንችስኮስ በቤተክርስቲያን እና በህብረተሰብ ውስጥ የሴቶችን ሚና አጉልተው አሳይተዋል! ር.ሊ.ጳ. ፍራንችስኮስ በቤተክርስቲያን እና በህብረተሰብ ውስጥ የሴቶችን ሚና አጉልተው አሳይተዋል!   (ANSA)

ር.ሊ.ጳ. ፍራንችስኮስ በቤተክርስቲያን እና በህብረተሰብ ውስጥ የሴቶችን ሚና አጉልተው አሳይተዋል!

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ በቤተክርስቲያን ውስጥ በሴቶች ላይ በተካሄደው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ንግግር አድርገዋል፣ የሴቶችን መብትና ክብር ለማጎልበት አንድነት እና ትምህርት እንዲሰጥ የሴቶችን አስተዋፅዖ እውቅና መስጠት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

የእዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ “ሴቶች በቤተ ክርስቲያን፡ የሰብዓዊነት ገንቢዎች” በሚል ርዕስ በተካሄደው የዓለም አቀፍ ጉባኤ ተሳታፊዎች በሙሉ ባደረጉት ንግግር ሞቅ ያለ ሰላምታ አቅርበዋል፤ በስብሰባው ላይ በመገኘታቸውና ጉባሄውን በማዘጋጀታቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

"ቤተክርስቲያኗ ይህንን ማስታወስ አለባት ምክንያቱም ቤተክርስቲያን እራሷ ሴት ናት: ሴት ልጅ፣ ሙሽራ እና እናት ናት" ብለዋል ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ።

በእግዚአብሔር ህዝብ ውስጥ የሴቶችን አስተዋፅዖ እውቅና መስጠት እና ዋጋ መስጠት ያለውን ፋይዳ ገልፀው ይህንን አላማ ከግብ ለማድረስ አንድነት፣ ማስተዋል እና ትብብር እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።

ከመላው አለም የተውጣጡ ግለሰቦችን የሚሰበስበው ጉባኤው የአስር ሴቶችን አርአያነት ያለው ቅድስና በማጉላት ላይ ያተኮረ ሲሆን እነሱም ጆሴፊን ባኪታ፣ ማግዴሊን ዘ ኢየሱስ፣ ኤልዛቤት አን ሴቶን፣ ሜሪ ማኪሎፕ፣ ላውራ ሞንቶያ፣ ካትሪ ተካኪታ፣ የካልካታዋ ቴሬሳ፣ ራፋካ ፒትራ ቾቦክ አር - ሬይስ፣ ማሪያ ቤልትራሜ ኳትሮቺ እና ዳፍሮሴ ሙካሳንጋ ይገኙበታል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ በሴት ብልሃት አማካኝነት የእግዚአብሔርን ቅድስና ልዩ ነጸብራቅ የሚያሳዩ የበጎ አድራጎት፣ ትምህርታዊ እና የጸሎት ተነሳሽነቶችን አስፈላጊነት አስምረውበታል።

ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ “የሴቶች አስተዋፅዖ ከምንጊዜውም በላይ አስፈላጊ ነው” ሲሉ አጽንኦት ሰጥተው ገልጸው፣ ዛሬ ባለው ዓለም የጥላቻ፣ የአመጽ እና የርዕዮተ ዓለም ግጭቶች ተግዳሮቶች መሆናቸውን አምነዋል።

በልስላሴ እና ርህራሄ የሚለይ የሴቶች አስተዋፅዖ በአስቸኳይ እንደሚያስፈልግ ተናግረው አንድነትን ለማጎልበትና የሰው ልጅን እውነተኛ ማንነት ለመመለስ አስተዋጾ እንደሚያደርጉ ገልጸው በትምህርት ጉዳይ ላይ በጉባኤው እና በተለያዩ የካቶሊክ ትምህርት ተቋማት መካከል ያለውን ትብብር አድንቀዋል።

"ተማሪዎችን የቅድስና ምስክርነቶችን በተለይም የሴት ቅድስናን ለማቅረብ የሚደረገው ጥረት ከፍ ያለ ዓላማ እንዲኖራቸው ሊያበረታታ ይችላል" ያሉት ቅዱስነታቸው መጪውን ትውልድ ለማነሳሳት አርአያነት ማቅረብ አስፈላጊ መሆኑን አሳስበዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ንግግራቸውን ሲያጠቃልሉ በዓለም ዙሪያ ሴቶች የሚገጥሟቸውን ትግሎች፣ ጥቃት፣ ኢኩልነት እና ኢፍትሃዊነትን በማንሳት እነዚህን ችግሮች ለመፍታት የተቀናጀ ርብርብ እንደሚያስፈልግ ጠቁመው፣ ሴት ልጆችና ወጣት ሴቶች የትምህርት ለውጥ የሚያመጣውን ሁለንተናዊ የሰው ልጅ ልማት ለማሳደግ ያለውን አቅም አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ንግግራቸውን በማጠቃለል የሴቶችን መብትና ክብር ለማስጠበቅ ቀጣይ ቁርጠኝነትን ከማሳየታቸው በፊት የጉባኤውን ውጤት ለጌታ ሰጥተው ለጉባሄው ተሳታፊዎች ሐዋርያዊ ቡርኬ ከሰጡ በኋላ ቅዱስነታቸው መልእክታቸውን አጠናቀዋል።  

 

08 March 2024, 16:31