ፈልግ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ወጣቶችን ሲያገኙዋቸው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንሲስ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ወጣቶችን ሲያገኙዋቸው  

“ከአፍሪካ ላይ እጃችሁን አንሱ!” የሚለው የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት አዲስ መጽሐፍ በየመደብሮቹ ተሰራጭቷል

በምዕራባውያን ኃያላን እየቀጠለ ያለውን አፍሪካን የመበዝበዝ አባዜ የሚያወግዘው እና መግቢያው ላይም የዕውቋ የናይጄሪያ የሴቶች መብት ተከራካሪ የሆነችው ቺማማንዳ ንጎዚ አዲቺ ፅሁፍ የሰፈረበት የርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቺስኮስ አዲስ መፅሃፍ በገበያ ላይ ውሏል።

አዘጋጅ ዘላለም ኃይሉ አዲስ አበባ

እጃችሁን ከአፍሪካ ላይ አንሱ!” ‘አፍሪካን አንቆ መያዝ ይቁምለመበዝበዝ የተዘጋጀች የማዕድን ቦታ አይደለችም ወይም ለመቀማት እና ለመዘረፍ የተዘጋጀች ምድር አይደለችም። አፍሪካ የራሷ እጣ ፈንታ ዋና ተዋናይ ትሁን!”

እነዚህ ቃላቶች ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቺስኮስ በዚህ ዓመት መጀመሪያ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ባደረጉት ጉብኝት የመጀመሪያ ቀን ላይ የተናገሩት ቃላት ናቸው።

የቫቲካን አሳታሚ ድርጅት አዲስ መጽሃፍ መለቀቁን ያሳወቀ ሲሆን ይህ በጣሊያንኛ የተፃፈ እናእጆቻችሁን ከአፍሪካ ላይ አንሱየሚል አርዕስት የተሰጠው መጽሃፍ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ከዚያም በደቡብ ሱዳን ባደረጉት ሃዋሪያዊ ጉዞ ወቅት ያደረጓችውን ንግግሮች ያካተተ እንደሆነም ተነግሯል።

ዋናው ነገር ግን መጽሐፉ የጳጳሱን ድምጽ ብቻ ሳይሆን ያካተተው በጉዞው ወቅት ያገኟቸውን እና ያናገሯቸውንም ሰዎች ሃሳቦች ጭምር ይዟል። በአሰቃቂ ግጭት ምስቅልቅላቸው የወጣው እነዚህ ሁለቱ ሃገራት ማለትም በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና በደቡብ ሱዳን - ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቺስኮስ የጦርነት ሰለባዎችን ምስክርነት እና ታሪኮቻቸውን በዚያን ወቅት አድምጠው የነበረ ሲሆን ይህም በመጽሃፋቸው ውስጥ ተካተዋል።

የመፅሃፉ መቅድም የተጻፈው በናይጄሪያዊቷ የሴቶች መብት ተከራካሪዋ እና ደራሲ ቺማማንዳ ንጎዚ አዲቺ ሲሆን ስለ መጽሐፉም ስትናገርለኮንጎ ህዝብ እና እኔ ቤቴ ብዬ የምጠራት የአፍሪካ አህጉር ውስጥ ለሚኖሩ ተወዳጆች እና ልባቸው ለተሰበረባቸው ህዝቦች ትንሽ ተስፋ ሰጥቶኛልብላለች።

ሃዋሪያዊ የሠላም ጉዞ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቺስኮስ በዲሞክራቲክ ሪፕብሊክ ኮንጎ እና ደቡብ ሱዳን በዚሁ ዓመት ከጥር 31 እስከ የካቲት 5 ቀን ሃዋሪያዊ ጉዞ ማድረጋቸው ይታወቃል።

ሃዋሪያዊ የሠላም ጉዞሲሉ የገለጹት እና አንድ ሳምንት የፈጀው ይህ ጉብኝት ግጭት ባለባቸው ሀገራት ዕርቀ ሠላም እንዲሰፍን እንዲሁም ከውጭ ጣልቃ ገብነት ነፃነታቸውን እንዲያውጁ ለማበረታታት ያለመ ጉዞ ነበር።

በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከመንግስት ባለስልጣናት ጳጳሳት እና ወጣቶች ጋር ተገናኝተው ሲናገሩ “‘የአፍሪካ የፖለቲካ ቅኝ ግዛትወደኢኮኖሚያዊ ቅኝ ግዛትየተሸጋገረ ሲሆን ይህም የባርነት አገዛዝ ጋር እኩል ነውብለዋል ብጹእነታቸው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ደቡብ ሱዳን ውስጥ በመጣላት ላይ ያሉ ፖለቲከኞችንም በማናገር እርስ በእርስ የሚያደርጉት ግጭት ሀገሪቷ ላይ ከባድ ውድመት እንዳደረሰ እና አሁንከዚህ በኋላ ይበቃልየሚባልበት ጊዜ እንደሆነ አበክረው ተናግረዋል።

ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና የዓለም ዝምታ

አዲቺ በመጽሃፉ መግቢያ ጽሁፏ ላይ እንዳስቀመጠችው በተለይም የርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳቱን ወደ ኮንጎ ባደረጉት ጉዞ ላይ ያተኮረች ሲሆንሀብቷ ለረጅም ጊዜ ሲበዘበዝ የኖረች ሀገር በዘረፋ እና በግጭት የተዳከመች ሀገር እንዲሁም እንደገና ለማገገም ተስፋ የምትቆርጥ ሀገርበማለትም ገልፃለች።

የሁኔታው ትልቁ አሳዛኝ ነገርትላለች አዲቺ አፍሪካን ይበልጥ የሚጎዳው የእርስ በርስ ግጭቱ ብቻ ሳይሆን የዓለም ዝምታ እና የአፍሪካን ሀብት በስግብግብነት የሚዘርፈው ዓለም የሚያደርጉት የአፍሪካን ሰብዓዊነት የሚያዋርደው ንግግራቸው ነውትላለች። በዚህ ዐውደ-ጽሑፍ የርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቺስኮስ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጉብኝት እና በዚያ ያስተላለፉትኃይለኛመልእክቶች ለበለጸጉ አገሮች እንደአስፈላጊ ተግሣጽይነበባሉ ትላለች።

አዲቺ ንግግሯ በመቀጠል፣የእርሳቸው መልእክት ለኮንጎ ብቻ ሳይሆን ለአጠቃላይ አፍሪካም አስፈላጊ ነው ነገር ግን ይህ በአንድ ምክንያት ብቻ አይደለም ዓለም አቀፉ ሰሜናዊው ክፍል የተመካበት ለሃብቷ ብቻ ሳይሆን እንዲሁም አህጉሪቱን በመፍራት አይደለም በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅት እንደተከሰተው ሁሉ የምዕራባውያን የውክልና ጦርነቶች ቦታ ዳግም ልትሆን ትችላለች በማለትም አይደለም ነገር ግን በቀላሉ በሰዎች ምክንያት ነው አህጉሪቷ ላይ ለሚኖሩ ለሰው ልጆች በሙሉ ሲባል ነው አፍሪካ አስፈላጊ የምትሆነው።በማለት ሃሳቧን አጠቃልላለች።  

23 May 2023, 14:18