ር. ሊ. ጳ. ፍራንችስኮስ ለሐዋርያዊ ጉብኝታቸው መሳካት የቅድስት ድንግል ማርያምን እገዛ ተማጸኑ።
ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ከዚህ በፊትም ዓለም አቀፍ ሐዋርያዊ ጉብኝት ከማድረጋቸው አስቀድመው በሮም ከተማ ወደ ሚገኘው ወደ ታላቁ ቅድስት ማርያም ባዚሊካ በመሄድ ጸሎታቸውን እንደሚያደርጉ ይታወቃል። በዚህ መሠረት ወደ ሊቷኒያ፣ ሌቶኒያንና ኤስቶኒያን ከሚያደርጉት ሐዋርያዊ ጉብኝት ሁለት ቀናት አስቀድመው ወደ ታላቁ ቅድስት ማርያም ባዚሊካ በመሄድ ጸሎታቸውን ማድረሳቸውን የቅድስት መንበር የሕትመት ክፍል ዳይሬክተር የሆኑት ክቡር አቶ ግሬግ ቡርኬ በትዊተር ማሕበራዊ መገናኛ ድረ ገጻቸው አስታውቀዋል።
20 September 2018, 16:28