ር.ቃ.ጳ. ፍራንቸስኮ፡ “ጠንካራ በሆነው በእግዚኣብሔርፍ ኃያል መተማመናችንን እንቀጥል!”
ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮስ በሰኔ 10/2010 ዓ.ም የብስራተ ገብርኤል ጸሎት ከምዕመናን ጋር ከመድገማቸው በፊት በዕለቱ ቅዱስ ወንጌል ላይ ተመርኩዘው ባደርጉት አስተንትኖ እንደ ገለጹት “ጠንካራ በሆነው በእግዚኣብሔርፍ ኃያል መተማመናችንን እንቀጥል” ማለታቸው ተገለጸ።
ቅዱስነታቸው ይህንን የተናገሩት በትላንትናው እለት ማለትም ማለትም በሰኔ 10/2010 ዓ.ም በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለተሰበሰቡ ምዕመናን እና የሀገር ጎብኚዎ በእለቱ በላቲን ስርዓተ አምልኮ አቆጣጠር ደንብ መሰረት ከማርቆስ ወንጌል 4፡26-34 ላይ ትወስዶ በተነበበው የአዳጊው ዘር እና የሰናፍጭ ዘር ምሳሌ ላይ ትኩረቱን ባደርገው አስተንትኖ እንደ ነበረ ለመረዳት ትችሉዋል።
የዚህ ዜና አጠናቃሪ መብራቱ ኃይሌጊዮርጊስ ቫቲካን
ክቡራን እና ክቡራት አድማጮቻችን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ በትላንትናው እለት ማለትም በሰኔ 10/2010 ዓ.ም በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለተሰበሰቡ ምዕመናን እና የሀገር ጎብኚዎች ያደርጉትን አስተንትኖ ሙሉ ይዘቱን እንደ ሚከተለው ተርጉመነዋል። አብራችሁን በመሆን እንድትከታተሉን ከወዲሁ እንጋብዛለን።
17 June 2018, 11:54