ፈልግ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በቫቲካን የቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በቫቲካን የቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ  (AFP or licensors)

ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮስ፡ ቤተሰብ በሕይወት ቤተ መቅደስ ውስጥ የእግዚኣብሔር ሥራ ተባባሪ ነው

መላው መጥምቁ ዮሐንስ የተወለደበት ሁኔታ በሚያስደንቅ የደስታ ስሜት የፈጠረ፣ ድንገተኛ እና ምስጋን የተቸረው ሁኔታ ነበረ።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ፡ ቤተሰብ በሕይወት ቤተ መቅደስ ውስጥ የእግዚኣብሔር ሥራ ተባባሪዎች ናቸው ማለታቸው ተገለጸ።

ቅዱስነታቸው ይህንን የተናገሩት በሰኔ 17/2010 ዓ.ም በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለተሰበሰቡ ምዕመናን እና የሀገር ጎብኚዎ በእለቱ በላቲን ስርዓተ አምልኮ አቆጣጠር ደንብ መሰረት ሉቃስ ወንጌል 1፡57-66.80 ላይ ትወስዶ በተነበበው የመጥመቁ ዩሐንስ ውልደት በተመለከተ በሚተርከው የመጽሀፍ ቅዱስ ክፍል ላይ ትኩረቱን ያደርገ እንደ ሆነ ለመገንዘብ ተችሉዋል። በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ስርዓተ አምልኮ ደንብ መስረት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ፣ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማሪያም እና የመጥቁ ዩሐንስ ልደቶች ብቻ የሚከበሩ ሲሆን የሌሎች ቅዱሳን ልደት በቅዱስ ዩሐንስ ልደት ውስጥ ተጠቃሎ የሚከበር እንደ ሆነም ለመረዳት ተችሉዋል።

ክቡራን እና ክቡራት አድማጮቻችን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸሶስ በትላንትናው እለት ማለትም በሰኔ 17/2010 ዓ.ም በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለተሰበሰቡ ምዕመናን እና የሀገር ጎብኚዎች በእለቱ ቅዱስ ወንጌል ላይ ተምስርተው ያደርጉትን የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ ሙሉ ይዘት እንደ ምከተለው እንቀርበዋለን፣ አብራችሁን በመሆን እንድተከታተሉ ከወዲሁ እናጋዝባዛለን።

“ የተወዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንደምን አረፈዳችሁ!”

“የዛሬው ዕለት ስረዓተ አምልኮ የመጥመቁ የቅዱስ ዮሐንስ ልደት እንድናካበር ይጋብዘናል። የእርሱ መወለድ የወላጆቹን ኤልሳቤጥ እና የዘካሪያስን ሕይወት እንዲበራ ያደርገ ሁኔታ ሲሆን ዘመዶቻቸውን እና ጎሬቤቶቻቸውን መደሰት እና መገረም ያካትታል። እነዚህ አረጋዊያን የነበሩ የእርሱ ቤተሰቦች ሕልም የነበራቸው ሰዎች የነበሩ እና ለእዚያም ቀን ዝግጁ የነበሩ ሰዎች ቢሆኑም፣ ነገር ግን ልጅ ስላልነበራቸው ያንን ቀን በተስፋ መጠበቅ አቁመው ስለነበረ፣ የመገለል፣ የውርደት፣ ተስፋ የመቁረጥ ስሜት ደርሶባቸው ነበር። አንድ ወንድ ልጅ እንደ ሚወልድ በተነገረው ወቅት ዘካሪያስ በጣም ተገርሞ ነበረ ምክንያቱም በጣም አርጅቶ ነበረ፣ ሁለቱ ቢሆኑ እድሜ ጠገብ ነበሩ፣ የተፈጥሮ ሕግጋት አይፈቅዱላቸውም ነበረና። በእዚህም የተነሳ ይህንን ጉዳይ አላመነም ነበር፣ ባለማመኑ የተነሳ ደግሞ ዲዳ እንዲሆን ተደረገ። ይህ ምልክት ነበረ። ነገር ግን እግዚአብሔር በሰው አስተሳሰብ እና በሰው ውስን የሰብአዊ ችሎታዎች ላይ አይወሰንም። በእግዚኣብሔር መተማመን እና በእግዚኣብሔር ምስጢር ፊት በዝምታ መጠበቅ መልካም የሆነ ነገር ነው፣ በትህትናን እና በዝምታ የእርሱን ተግባር መጠባበቅ ይሻላል፣ ይህ ተግባሩ በታሪክ በተደጋጋሚ የተከሰተና የሰው ልጆች ከሚያስቡት በላይ ብዙ ታላቅ ነገር አድርጉዋል። እናም አሁን በኤልሳቤጥ እና በዘካርያስ ሕይወት ውስጥ የተከናወነው ሁኔታ "ለእግዚአብሔር ምንም ነገር እንደ ማይሳነው" ተረድተው ለእርሱ ትልቅ ክብር ሲሰጡ እናያለን። ዛሬ የተነበበልን ቅዱስ ወንጌል (ሉቃስ 1፡57-66.80) የሕጻኑን መወለድ ካበሰረ በኃላ በመቀጠል ለልጁ ስለሚወጣለት ስም ይናገራል። ኤሊሳቤጥም ከባሕላቸው ውጪ አስገራሚ በሆነ መልኩ በመሄድ ስሙ “ዩሐንስ ተብሎ ይጠራል” በማለት ይህ ሕጻን አሁን በእዝህ እድሜ ያልተጠበቀ በመሆኑ የተነሳ ነጻ የእግዚኣብሔር ስጦታ በማለት ትሰይመዋለች፣ ምክንያቱም ዩሐንስ ማለት ነጻ “እግዚአብሔር ጸጋን ሰጠን” ማለት ነው። እንዲሁም ይህ ሕፃን ጠንካራ እና በትዕግሥት የእግዚአብሔር ጸጋ ለሚጠባበቁ ለድሆች ምስክር ነው። ዚካሪያስም ባልተጠበቀ መልኩ ለሕጻኑ የመጠሪያ ስም ለማውጣት ሰሌዳ እንዲሰጡት ጠይቆ በእዚያ ላይ የልጁን ስም ጻፈ፣ ምክንያቱም ዲዳ ስለነበረ ነው፣ እናም “ወዲያውም አፉ ተከፈተ፤ አንደበቱ ተፈታ፤ እግዚአብሔርንም እያመሰገነ መናገር ጀመረ”። መላው መጥምቁ ዮሐንስ የተወለደበት ሁኔታ በሚያስደንቅ የደስታ ስሜት የፈጠረ፣ ድንገተኛ እና ምስጋን የተቸረው ሁኔታ ነበረ። ድንገተኛ፣ አስደናቂ እና ምስጋን። ሕዝቡ በታላቅ አግራሞት በመደነቅ “ጎረቤቶቹም ሁሉ በፍርሀት ተሞሉ፤ ይህም ሁሉ ነገር በደጋማው የይሁዳ ምድር ሁሉ ተወራ”። ወንድሞች እና እህቶች አማኛ የሆነው ሕዝብ አንድ የተደበቀ እና ትሁት የሆነ አንድ ታላቅ ነገር እንደ ተከሰተ ነገር እንደ ነበረ ስላወቀ “ይህ ሕፃን ምን ሊሆን ይሆን?” በማለት ይጠይቃል። የእግዚአብሄር ታማኝ ህዝቦች በእምነት፣ በመደነቅ እና በመገረም እምነትነቱን በደስታ መኖር ይችላል። በእዚያ የነበሩ ሕዝቦች በተከሰተው ታላቅ በሆነው ነገር ተገርመው ስያወሩ የነበሩትን ነገር እንመልከት፣ በምጥመቁ ዩሐንስ መወለድ የተነሳ ሕዝቡ ደስታ ሲሰማው፣ በጣም ሲገረም፣ በመደነቅም ጭምር በምስጋና ሲደሰት እናያለን። ይህን በመመልከት “የእኔ እምነት እንዴት ነው? ብለን ልንጠይቅ ይገባል። እምነቴ በደስታ የተሞላ ነው ወይስ እንዲያው ሁሌ ተመሳሳይ በሆነ እና ወጥ በሆነ መንገድ ላይ ብቻ ነው እየተጓዘ የሚገኘው? የእግዚኣብሔርን ድንቅ የሆነ ሥራ ስመለከት እደሰታለሁ ወይ? ስለስብከተ ወንጌል አገልግሎት ስሰማ ወይም ደግሞ የአንድን ቅዱስ ሰው ሕይወት ስመለከት፣ ወይም በጣም ብዙ መልካም የሚባሉ ሰዎችን ስመለከት የጸጋ ስሜት በውስጤ ወይ? ወይስ ምንም ነገር በልቤ አይንቀሳቀስም? ከመንፈስ ቅዱስ የሚገኝ ማጽናኛን ይሰማኛል ወይስ የተዘጋው ነኝ? እያንዳንዳችን የሕሊናችንን ምርመራ በማድረግ “እምነቴ እንዴት ነው? ለእግዚኣብሔር ድንቅ ተግባር ክፍት ነው ወይ? በማለት ራሳችንን እንጠይቅ፡ ምክንያቱም እግዚኣብሔር ሁሌም የሚያስገርመን አምላክ ነውና። የእግዚአብሔርን በሕይወቴ መገኛቱን በሚያስደንቅ ሁኔታ በአድናቆት ስሜት ውስጥ ሆኜ "አጣጥሜያለሁ" ወይ? የእመነት ቃላት የሆኑትን ደስታ፣ የመገረም ስሜት፣ የመደነቅ እና የማመስገን ስሜቶችን ልናጣጥም ይገባናል። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም በእያንዳንዱ ሰው ውስጥ የሕይወት ምንጭ የሆነው እግዚኣብሔር እንደ ሚገኝ ማመን እንችል ዘንድ ትርዳን። የእግዚኣብሔር እና የእኛ እናት የሆነችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማሪያም ቤተሰቦች ልጆቻቸውን በማሳደግ ሂደት ውስጥ የእግዚኣብሔር የሥራ ተባባሪ መሆናቸውን እንዲገነዘቡ ትርዳቸው። እያንዳንዱ ቤተሰብ በሕይወት ቤተ መቅደስ ውስጥ የእግዚኣብሔር ተባባሪዎች ናቸው እያንዳንዱ ሕጻን በሚወለድበት ወቅት የደስታ፣ የመደነቅ ኣና የምስጋና ስሜት ሊፈጥር ይገባዋል። ”

24 June 2018, 14:41