ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮስ፡ ራሳችንን ለኢየሱስ አስገዝተን መኖር ይኖርብናል!
በእዚህ በፋሲካ በዓል ስሞን የሚነበቡልን የእግዚኣብሔር ቃላት ከሙታን የተነሳው ጌታ ማኅበር አባል እንድንሆን የሚያስችሉንን የአኗኗር ዝይቤ ያመለክቱናል።
ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮስ፡ ራሳችንን ለኢየሱስ አስገዝተን መኖር ይኖርብናል!
የጎርጎሮሳዊያኑን የቀን አቆጣጠር በሚከተሉ የክርስቲያን ማኅበረሰቦች ዘንድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን የተነሳበት የፋሲካ ወይም የትንሳኤ በዓል ከተከበረ እነሆ በስድስተኛው የፋሲካ የትንሳኤ ሳምንት ላይ እንደ ምንገኝ ይታወቃል። ይህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ የተነሳበት ስድስተኛው የፋሲካ ሳምንት ሰንበት በሚያዝያ 28/2010 ዓ.ም. በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ መሪነት ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ተከብሮ ማለፉ ታውቁዋል። ቅዱስነታቸው በወቅቱ ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ላይ ያስሙት ስብከት መሰረቱን አድጎ የነበረው “በፍቅሬ ኑሩ” በሚለውን ከዩሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 15:9 በተጠቀሰው በኢየሱስ ቃል ላይ መሰረቱን ያደርገ እንደ ነበረ ለመረዳት ተችሉዋል።
ክቡራት እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በሚያዝያ 28/2010 ዓ.ም. በቫቲካን በሚገኘው የቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ላይ ያስሙትን ስብከት ሙሉ ይዘት እንደ ሚከተለው ተርጉመነዋል አብራችሁን በመሆን እንድትከታተሉ ከወዲሁ እንጋብዛለን።
06 May 2018, 10:29