ፈልግ

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በቫቲካን የቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በቫቲካን የቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ  (Vatican Media)

ር.ሊ.ጳ ፍራንቸስኮስ “ምስጢረ ጥምቀት ክፉ መንፈስን የማሸንፊያ መሳሪያ ነው”

ር.ሊ.ጳ ፍራንቸስኮስ ረቡዕ የሚያዝያ 17/2010 ዓ.ም. ባደረጉት የጠቅላላ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ እንደ ገለጹት “ምስጢረ ጥምቀት ክፉ መንፈስን የማሸንፊያ መሳሪያ ነው” ማለታቸው ተገለጸ።

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ ዘወትር ረዕቡ እለት በቫቲካን በሚገኘው የጳውሎስ 6ኛ አዳራሽ ወይም ደግሞ እንዳስፈላጊነቱ እና እንደ አየሩ ሁኔታ በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለሚሰበሰቡ ምዕመናን እና የሀገር ጎብኝዎች በተለያዩ አርእስቶች ላይ ተመርኩዘው የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ እንደ ሚያደርጉ ይታወቃል። የእዚሁ መርሃ ግብር አንዱ አካል በሆነው በሚያዝያ 03/2010 ዓ.ም. ረፋዱ ላይ ያደረጉት በምስጢረ ጥምቀት ዙሪያ ላይ ባተኮረው የክፍል አንድ የትምህርተ ክርስትሶስ አስተምህሮ “ምስጢረ ጥመቀት የክርስትና ሕይውት መሰረት ነው” ማለታቸውን መገለጻችን ይታወሳል። ባልፈው ሳምንት ማለትም በሚያዝያ 10/2010 ዓ.ም. በምስጢረ ጥምቀት ዙሪያ ባደርጉት የክፍል ሁለት አስተምህሮ ምስጢረ ጥምቀት “ምስጢረ ጥምቀት የክርስትና እምነት ምልክት ነው” ማለታቸውን መዘገባችን የሚታወቅ ሲሆን በዛሬው እለት አሁንም በምስጢረ ጥምቀት ዙሪያ ባደርጉት ክፍል ሦስት የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ ምስጢረ ጥምቀት “ክፉ መንፈስን የማሸንፊያ መሳሪያ ነው” ማለታቸው ተገልጹዋል።

የእዚህ ዝግጅት አጠናቃሪ መብራቱ ኃይሌጊዮርጊስ ቫቲካን

በእለቱ የተነበበው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል “ማጣትን ዐውቀዋለሁ፤ ማግኘትንም ዐውቀዋለሁ። ብጠግብም ሆነ ብራብም፣ ባገኝም ሆነ ባጣ በማንኛውም ሆነ በየትኛውም ሁኔታ ያለኝ ይበቃኛል የማለትን ምስጢር ተምሬአለሁ። ኀይልን በሚሰጠኝ በእርሱ ሁሉን ማድረግ” (ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 4፡12-13)።

ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ታዳሚዎች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ በምስጢረ ጥምቀት ዙሪያ ላይ አድርገውት የነበረውን የትምሕርተ ክርስቶስ አስተምህሮ ሙሉ ይዘቱን እንደ ሚከተለው ተርጉመነዋል፣ አብራችሁን በመሆን እንድተከታተሉን ከወዲሁ እንጋብዛለን።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንደምን አረፈዳችሁ

“በእግዚኣብሔር ቃል ላይ ተመስርተን በምስጢረ ጥምቀት ዙሪያ የጀመርነውን አስተንትኖ ዛሬም እንቀጥላለን። ለንዑሰ ክርስቲያንን ብርሃን የሚሆነው እና እምነታቸውን የሚያነሳሳው ቅዱስ ወንጌል ነው፡ “ከጥምቀት ተለይቶ የማይታየውን የእምነት ምላሽ እንዲሰጡ ያስችላቸዋል። ወደ እመንት ሕይወት የሚደረግ ምስጢራዊ አገባብ በመሆኑ በእርግጥ ጥምቀት በልዩ ሁኔታ “የእምነት ምስጢር ነው’” (የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ክርስቶስ ቁ.1236)። እምነት “በውስጡ የሚፈልቅ የዘላለም ሕይወት ውሃ ምንጭ” (ዩሐንስ 4፡14) ለሆነው እና “የዓለም ብርሃን” (ዩሐንስ 9:5)፣ “ትንሣኤና ሕይወት” (ዩሐንስ 11፡25) ለሆነው ጌታ ኢየሱስ ራሳችንን ማስረከብ ማለት ነው። ንዑሰ ክርስቲያን የሕይወት ውሃ የተጠማችሁን የሳምራዊቱዋን ሴት ተመክሮ በመከተል ዓይነ ስውር ሆኖ የተወለደውን ሰው ብርሃን ይመለከት ዘንድ ዓይኑን የከፈተውን፣ አልዓዛርን ከመቃብር ውስጥ እንዲወጣ ያደረገውን ኢየሱስን እንዴት ማዳመጥ እንደ ሚገባቸው፣ የእርሱን አስተምህሮ እና የእርሱን ተግባር በሚገባ የተማሩ ናቸው። ቅዱስ ወንጌልን በእመንት የሚቀበሉ ሰዎች በክፉ መንፈስ ላይ የበላይነት እንዲቀናጁ በማድረግ ጌታን በደስታ እና በአዲስ ሕይወት ማገልግልን እንዲማሩ ኃይል የሰጣቸዋል። ምስጢረ ጥምቀት ወደ ምስጥበት ገንዳ የሚኬደው በባዶ እጅ ሳይሆን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ባሉ ሰዎች ጸሎት በመታጀብ፣ የቅዱሳንን ሊጣኒያ በመድገም፣ በጸሎት በመታጀብ እና ንዑሰ ክርስቲያን የሚቀቡት ቅባቅዱስን በመያዝ ነው። ይህም ከጥንት ጊዜያት ጀምሮ ቤተ ክርስቲያን የምታደርገው ጸሎት የእግዚኣብሔር ልጅ ለመሆን ዳግም ለመወለድ የሚዘጋጁትን ሰዎች የቤተክርስቲያኒቷ ጸሎት ከክፉ ነገሮች ጋር የሚደረገውን ውግያ እንዲያሸንፉ የሚረዳቸው፣ በመልካም ጎዳና ልይ እንዲራመዱ አብሮዋቸው የሚሆን፣ ከኃጢያት ኃይል እንዲያመልጡ እና የመለኮታዊ መንግሥት ጸጋ ተካፋይ እንድሆኑ ይረዳቸዋል። ከእዚያም ካህኑ ጎላማሳ ለሆኑ ተጠማቂውን በንዑሰ ክርስቲያን ዘይት ይቀባዋል (የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ክርስቶስ ቁ.1237) ይህም ማለት ከክርስቶስ ከሚለየያዩ ነገሮች እንዲላቀቅ እና ከእርሱ ጋር የጠለቀ ግንኙነት እንዳይደረግ ከሚያድርግ ነገሮች ሁሉ ነፃ የሚያወጣ ጸሎት ነው። ለሕጻናትም ቢሆን ከአዳም እና ከሄዋን ከወረሱስት ኃጢኣት እግዚኣብሔር ነጻ እንዲያወጣቸው እና የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያዎች እንዲሆኑ ይባረካሉ። ቅዱስ ወንጌል እንደ ሚመሰክረው ኢየሱስ ራሱ የእግዚአብሔርን መንግሥት መምጣት ለማሳየት ተዋግቶ አጋንንትን አስወጣ (ማቴዎስ 12:18) በክፉ ኃይል ላይ የምንጎናጸፈው ድል ለእግዚአብሔር ጌትነት ነጻ የሆነ የሕይወት ዘመን ያስገኛል። ምስጢረ ጥምቀት አስማታዊ የሆነ ቀመር አይደለም፣ ነገር ግን “ከክፉ መንፈስ ጋር እድንዋጋ” የሚረዳን የመነፈስ ቅዱስ ስጦታ ሲሆን በእዚህ እግዚኣብሔር አንደኛ ልጁን ወደ ዓለም የላከው የሰይጣንን ኃይል እንዲሰባብር እና የሰው ልጆች ከነበሩበት ጨለማ ወጥተው ወደ እርሱ በዘላለማዊ ብርሃን ወደ ተሞላው ምንግሥት እንደ ሚመራን ማመን እንድንችል ያደርገናል። የክርስትና ሕይወት ከእግዚያብሄር፣ ከእርሱ ፈቃድ እና ከእርሱ ጋር ከነበረን ሕብረት በመለያየት ዓለማዊ ወደ ሆኑ እና ወደ ሚያታልሉን ነገሮች እንድንመለስ የምያባብሉን ፈተናዎች እንደ ሚገጥሙን ከተሞክሮ ወይም ከልምድ ለመረዳት እንችላለን። ከጸሎት በመቀጠል በንዑሰ ክርስቲያን ዝይት ደረት የመቀባት ስነ-ስረዓት ይደረጋል “ይህም የሚደረግበት ምክንያት ምስጢረ ጥምቀት ወደ ሚሰጥበት ገንዳ ከመቀረባቸው በፊት እና እንደ ገና ወደ አዲስ ሕይወት ከመመለሳቸው በፊት ሰይጣንን እና ኃጢአትን ለመካድ ጥንካሬ እንዲያገኙ ያደርጋል”። ዘይት በተፈጥሮ ይዘቱ ወደ ሰውነት ክፍሎች ውስጥ ዘልቆ መግባት በመቻሉ ምክንያት በጥንት ጊዜ የነበሩ ታጋዮች የጡንቻቸው ክፍል ቅርጽ ለማስያዝ እና ለጠላት እጃቸውን በቀላሉ ላለመስጠት ዘይት በሰውነታቸው ላይ ይረጩ ነበር። ይህንን ተምሳሌት በመጠቀም በጥንት ጊዜ የነበሩ ክርስቲያኖች በጳጳስ የተባረከ ዘይት በመጠቀም ንዑሰ ክርስቲያንን ይቀቡ ነበር ይህ ማለት ደግሞ “በእዚህ የድኽንነት ምልክት፣ አዳኝ በሆነው በክርስቶስ ኃይል በመበረታታት ከክፉ ነገሮች ጋር በመዋጋት ማሸነፍ የሚል ትርጉ አለው። ከክፉ መነፈስ ጋር መተገል፣ ከሚያታልሉን ክፉ ነገሮች ለማምለጥ፣ በጣም አድካሚ የሆነ ትግል ከተደረገ በኋላ ድካማችንን ለማስታገስ እንፈልጋለን ነገር ግን የክርስቲያን ሕይወት ሁልጊዜም ቢሆን በትግል የተሞላ መሆኑን የግድ ማወቅ ይኖርብናል። ብቻችንን እንዳልሆንም ማወቅ ይኖርብናል፣ የቤተ ክርስቲያን እናት የሆነችው በጥምቀት እንደ ገና የተወለዱ ልጆቹዋ በክፉ መነፈስ እንድይወሰዱ ነገር ግን እኛ ብቻ አይደለንም, የቤተክርስቲያን እናት የሆነችው በጥምቀት ዳግም የተወለዱ ልጆቹዋ በክፉ ኃይል እና በአደገኛ ሁኔታ ውስጥ ገብተው እንዳይሸነፉ ነገር ግን በክርስቶስ የፋሲካ ኃይል ድል እንዲያደርጉ ትጸልያለች፣ እናም ቅዱስ ሐዋሪያው ጳውሎስ የተናግረውን ቃል በእምነት በመቀበል በድጋሚ ከእርሱ ጋር በመሆን “ኀይልን በሚሰጠኝ በእርሱ ሁሉን ማድረግ” እችላለሁ ልንል ይገባል።”

25 April 2018, 10:54