ፈልግ

ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮስ፡ በቫቲካን በቅዱስ ጴጥሮስ ባዚሊካ በሚያዝያ 02/2010 ዓ.ም. ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮስ፡ በቫቲካን በቅዱስ ጴጥሮስ ባዚሊካ በሚያዝያ 02/2010 ዓ.ም. 

ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮስ፡ የሐዋርያት ምስክርነት የጀመረው ከኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳሄ በኃላ ነው።

ሁሉም ነገር የሚጀምረው ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳሄ በኃላ ነው፣

ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮስ፡ የሐዋርያት ምስክርነት የጀመረው ከኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳሄ በኃላ ነው።

ከኅዳር 29/2008 ዓ.ም እስከ ኅዳር 4/2009 ዓ.ም ድረስ (ለ349 ቀናት ያህል ማለት ነው) በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ የታወጀው እና በመላው ዓለም በምገኙ የካቶሊክ አብያተ ክርስቲያንት ዘንድ ቅዱስ ልዩ የምህረት አመት ተከብሮ ማለፉ ይታወቃል።

በኅዳር 11/2009 ልዩ ቅዱስ የምሕረት ዓመት በይፋ ሲጠናቀቅ የምሕረት ተግባራችንም በዚያ የሚጠናቀቁ አለመሆኑን በወቅቱ የገለጹት ቅዱስነታቸው ይልቁኑም መላው የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ምዕመን አካላዊ እና መንፈሳዊ የምሕረት ተግባራትን በምዕመናን ልብ ውስጥ በዘላቂነት ታትመው እስከ ሕይወታቸው ፋጻሜ ድረስ ከእነርሱ ጋር በመዝለቅ መፈሳዊ ገዴታችንን በምገባ እንድንወጣና በማቴዎስ ወንጌል 25.31-40 ላይ እንደ ተጠቀሰው በመጨረሻ የፍርድ ቀን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለምያቀርብልን ጥያቄ በብቃት መልስ እንድንሰጥ የምያስችለን ክርስትያናዊ ስንቆቻችን ሆነው ከእኛ ጋር እስከ መጨረሻው መዝለቅ ይገባቸዋል ማለተቻው ይታወሳል። በእነዚህ ለ349 ቀናት ያህል በቆዩት ቅዱስ ልዩ የምሕረት ዓመት በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ አነሳሽነት “የምሕረት ልዑካን” የሚል መጠሪያ የተሰጣቸው እና ከመላው የዓለማችን ክፍሎች የተውጣጡ 1000 የካቶሊክ ቤተ ክርስትያን ካህናትን ያቀፈው ልዩ የምሕረት ልዑኽ በቅዱስነታቸው መቋቋሙ የምታወቅ ስሆን እነዚህም ካህናት ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በተቀበሉት ምስጢረ ንስሐን እና ከምስጢረ ንስሓ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን መነፍሳዊ አገልግሎቶች በመስጠት የኃጢኣት ስርዬት የመስጠት ልዩ መንፈሳዊ መብት ተጠቅመው በመላው ዓለም በመጓዝ የምሕረት ተግባርትን ስያከናውኑ ቆይተዋል።

እነዚህ በቁጥር 1000 የሚሆኑ  “የምሕረት ልዑካን” የተሰጣቸውን መንፈሳዊ ተልዕኮ አጠናቀው ወደ ሮም ከተማ ተመልሰዋል። በሚያዝያ 02/2010 ዓ.ም. ረፋዱ ላይ በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ ባዚሊካ ተገኝተው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ መሪነት የተካሄደውን መስዋዕተ ቅዳሴ መታደማቸው ተገልጹዋል። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በወቅቱ ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ላይ ያሰሙት ስብከት እንደ ሚከተለው አስናድተነዋል አብራችሁን በመሆን እንድትከታተሉን ከወዲሁ እናጋብዛለን።

““ሐዋርያትም ስለ ጌታ ኢየሱስ ትንሣኤ በታላቅ ኀይል መመስከራቸውን ቀጠሉ” (የሐዋሪያት ሥ. 4፡33) የሚለውን በዛሬው እለት ከሐዋሪያት ሥራ ላይ ተወዶ የተነበበውን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል አዳምጠናል። ሁሉም ነገር የሚጀምረው ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳሄ በኃላ ነው፣ የሐዋርያት ምስክርነት የመነጨው ከእዚሁ ሲሆን በዚህ ምክንያት የማኅበረሰቡ አባላት እምነትና አዲስ ህይወት ግልጽ ከሆነው የወንጌል የአኑዋንዋር ዘይቤው የተገኙ ናቸው። የዛሬው ቀን መስዋዕተ ቅዳሴ ላይ የተነበቡት ምንባባት ውስጥ የተጠቀሱት ዳግም መወለድና የማህበረሰብ ህይወት የምባሉ ሁለት የማይነጣጠሉ ገፅታዎች እንዲፈጠሩ ያደርጋል። ስለዚህም የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ወደ እናንተ ስመለስ ከቅዱስ ልዩ የምሕረት አመት ጀመሮ ስለነበራቸው አገልግሎት ለማሰላሰል ፈልጋለሁ። እናንተ አከናውናችሁት የነበረው ተግባር በእነዚህ ከላይ በተጠቀሱት ሁለት ገጽታዎችን የሚመለከት አገልግሎት የነበረ ሲሆን ይህም ለሰዎች አገልግሎ በመስጠት “ሰዎች ከመንፈስ እንዲወለዱ” እና ለማኅበራዊ አገልግሎት ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ በማገዝ ሰዎች በደስታ እና ከፍቅር ትዕዛዝት ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ሕይወት እንዲኖር አግዛችኃል። ዛሬ የሰማነው የእግዚኣብሔር ቃል (የሐዋሪያት ሥራ 4፡32-37, የዮሐንስ ወንጌል 3:32-37) በእዚህ ረገድ የምያመለክተውን ሁለት አቅጣጫ እናንተ አሁን ያደርጋችሁትን አገልግሎት በተመለከተ ሁለት ነገሮችን ለማለት እወዳለሁ። የዛሬው ቅድሱ ወንጌል የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ከሙታን መነሳት መስካሪ እንዲሆን የተጠራ አንድ ሰው በቅድሚያ እርሱ ራሱ በቅድሚያ “ከመንፈስ መወለድ” (ዩሐንስ 3፡7) እንደ ሚኖርበት ይገልጻል። ይህ ካልሆነ ግን ልክ በዛሬው ቅዱስ ወንጌል ውስጥ በዋነኝነት እንደ ተጠቀሰው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኒቆዴሞስ “ወደ እግዚኣብሔር መንግሥት ለመግባት” “ዳግም መወለድ”፣ “ከውሃ እና ከመነፈስ መወለድ” ያስፈልጋል (ዩሐንስ 3፡3-5) ባለው ግባለው ጊዜ ኒቆዴሞስም ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል ብሎ በጠየቀው ወቅት ኢየሱስ አንተ የእስራኤል መምህር ሁነህ ስለእነዚህ ነገሮች እንዴት አታውቅም በሎ እንደ መለሰለት ዓይነት ሰው ይሖናል ማለት ነው። ኒቆዲሞስ ራሱን ዝቅ የሚያደርግ ሁሉ ከፍ ይላል፣ ኃለኞች ፊተኞች ይሆናሉ፣ በሽተኞች መሆናቸውን አውቀው ፈውስ የሚሹ ሁሉ ፈውስን ያገኛሉ የሚለውን ከእግዚኣብሔር አመክኒዮ ወይም አስተሳሰብ የመነጨውን የጸጋ እና የምሕረት አመክንዮ ወይም አስተሰሰብ ኒቆዲሞስ አልተረዳውም ነበር። ይህ ማለት በሕይወታችን ውስጥ የሚከሰቱ ማንኛውም ዓይነት ነገሮችን በቅድምያ ለእግዚኣብሔር አባት፣ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ እና ለመንፈስ ቅድሱ በአደራነት መስጠት ያስፈልጋል ማለት ነው። ማሳሰቢያ! ይህ ማለት “ሁሉንም ነገር ሙሉ የሆኑ” ከሰዎች ሁሉ በላይ የሆነ አስግራሚ የሆነ ክህሎት ያላቸው ካህነት መሆን ይኖርባችኃል እያልኩኝ እንዳልሆነ ልብ ልትሉ ይገባል። በፍጹም ዓይደለም እንዲሁ ተራ፣ ትሁት እና ሚዛናዊ የሆነ ካህን ነገር ግን ነገር ግን በቀጣይነት በመነፈስ ቅዱስ ለመታደስ ራሱን ያዘጋጀ፣ ጠንካራ የሆነ ኃይል የማይጠቀም፣ ውስጣዊ የሆነ ነጻነት ያለው፣ በተለይም ደግሞ ራሱን በራሱ ነጻ ያደርገ ወደ ፈለገው አቅጣጫ ወደ ሚንፈሰው የመነፈስ ቅዱስ ንፋስ እንዲወደው ራሱን ያዘጋጀ ካህን ማለቴ ነው። በኈለተኛ ደረጃ የምናየው አቅጣጫ ለማኅበረሰቡ የምታደርጉትን አገልግሎት የተመለከተ የሆናል፣ በእዚህ ረገድ በአሁኑ ዘመን ባለው ዓለማችን በፈጠረው የበረሃነት ስሜት ውስጥ የደኽንነት ምልክት ሆኖ በጽናት መቆም፣ ይህም ማለት የክርስቶስን መስቀል በመምሰል የመንፈሳዊ ለውጥ ምንጭ እና በአጠቃላይ የታደሰ ማኅበርሰብ ለመፍጠር እና ዓለምን ለማደስ መትጋት የሚለውን ያሳያል። በተለይ ደግሞ ለእኛ ሲል የሞተው እና ከሙታን የተነሳው የጌታ ኃይል በቤተክርስቲያን ውስጥ ሕብረት እንዲፈጠር እና በቤተክርስቲያን አማክይነት መላው የማኅበረሰብ ክፍል ኅብረትን እንዲፈጥር ኃይል የሚሰጠው እርሱ መሆኑን አፅንዖት ለመግለጽ እወዳለሁ። ኢየሱስ ራሱ መከራውን ከመቀበሉ በፊት “እኔ ግን ከምድር ከፍ ከፍ ባልሁ ጊዜ ሰውን ሁሉ ወደ ራሴ እስባለሁ። (ዩሐንስ 12:32) በማለት መናገሩ ይታወሳል። የእዚህ ዓይነቱ ሕበረት ደግም ከመጀመሪያ ጊዜ ከእየሩሳሌም አንስቶ በሐዋሪያት ሥራ 4:32 እንደ ተጠቀሰው ያመኑትም ሁሉ በአንድ ልብና በአንድ ሐሳብ ተስማምተው ነበር በማለት ከጥንት ጊዜ ጀምሮ የእዚህ ዓይነት ሕብረት እንደ ነበረ ይገልጻል። የእዚህ ዓይነቱ ሕብረት ተጨባጭ በሆነ መልኩ በመገለጽ እና በመኖር “ያላቸውን ሁሉ በአንድነት ይካፈሉ ነበር” ከኣነርሱም መካከል ማንም ሰው ችግረኛ አልነበረም ነበር” በማለትይገልጸዋል። ይህ በወቅቱ የነበረው የሐዋሪያት ሕብረት ቀሪውን የማኅበርሰብ ክፍል ያዳረሰ ሕብረት ነበር፣ ከሙታን የተነሳው ክርስትሶ ከእነርሱ ጋር በመሆኑ የተነሳ ሰዎችን መሳብ የሚችል ኃይል ፈጥሮ እንደ ነበረ በቤተክርስቲያን ምስክርነት አመካይነት እነ በተለያዩ መነገዶች በተሰራቸው መልካም ዜና የተነሳ ይህ ሕበረት ወአ ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች ተዳርሶ የነበረ ሲሆን ማንም ሰው ከእዚህ ውጪ እንዲሆን አልተድረገም ነበር። እናንተም ወንድሞኣቼ በእዚህ ዓይነቱ አገልግሎት ውስጥ በመሳተፍ ለየት ባለ ሁኔታ ለተለየ የምሕረት ተግባር አገልግሎት ስትሰጡ ቆይታችኃል። በእርስጥ ዛሬ ቤተ ክርስቲያን ትሁን በዛሬው ዘመን የሚገኘው ዓለማችን ለየት ባለ ሁኔታ ምሕረት የሚይስፈልጋቸው ሲሆን ምክንያቱም በክርስትሶ አማክይነት እግዚኣብሔር እንዲመጣ የፈለገው ሕብረት እንዲፈጠር የሚያግደው የክፉ መነፈስ በተልለያዩ መነገዶች እይተሰራጨ በመሆኑ የተነሳ፣ ምንም ኣንኳን አንድ አንዶቹ ጥሩ የሚባሉ ቢሆንም እናኳን ያለአግባብ ጥቅም ላይ በመዋላቸው የተንሳ ክፉ መንፈስን እያሰራጩ ይገኛሉ መልካም እና መልኮታዊ የሆኑ ነገሮችን ከምስደመጥ ይልቅ ክፉ ነገሮችን በመዝራት ላይ ይገኛሉ። “ሕበረት ማንኛውንም ጥላች የምሳወገጃ መሳሪያ መሆኑን በሚገባ እንገነዘባለን። ነገር ግን በተመሳሳይ መልኩ የላምሕረት የህንን ሕብረት ማስጠበቅ አስቸጋሪ ኣንደ ሆነም እናውቃለን ይህም በታሪክ ውስጥ እና በሕይወታችን የታየ ተጨባጭ እውነታ ነው። የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ከእዚህ መስዋዕተ ቅዳሴ በኃላ ወደ አገልግሎታችሁ በምትመለሱበት ወቅት በደስት ወደ ምህረት አገልግሎታችሁ ተመለሱ። በቅድሚያ እናንተ ራሳቹ ዳግም መወለድ እንደ ሚገባችሁ በማመን በኣግዚኣብሔር ፍቅር ተመኦልታችሁ የምሕረርት ተግባራትን ፈጽሙ። በተጨማሪም ተጨባጭ በሆነ መልኩ ከሙታን የተነሳውን ጌታ ምልክት በሰዎች ህያውት ውስጥ በማኖር የሕብረርት መሳሪያ ምልክት እንዲሆን አድርጉት። ”

10 April 2018, 09:48