ፈልግ

2019.03.08 SAN GIOVANNI DI DIO Gesù Cristo nel deserto tentato dal diavolo domenica di quaresiam

የመጋቢት 15/2016 ዓ.ም የመጀመሪያው የዐብይ ጾም ሳምንት ንባባት እና የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ

በዐብይ ጾም ወቅት የእግዚአብሄርን ድምጽ መስማት ይኖርብናል

 

የእለቱ ንባባት

1.    ኦሪት ዘፍጥረት 9፡8-15

2.    መዝሙር  24

3.    1 ጴጥሮስ 3፡18-22

4.    ማርቆስ 1፡12-15

የእለቱ ቅዱስ ወንጌል

ወዲያውም መንፈስ ወደ ምድረ በዳ አወጣው። በምድረ በዳም ከሰይጣን እየተፈተነ አርባ ቀን ሰነበተ ከአራዊትም ጋር ነበረ፥ መላእክቱም አገለገሉት። ዮሐንስም አልፎ ከተሰጠ በኋላ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ወንጌል እየሰበከና። ዘመኑ ተፈጸመ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች ንስሐ ግቡ በወንጌልም እመኑ እያለ ወደ ገሊላ መጣ።

የእለቱ ቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ

ዛሬ የዐብይ ጾም በተጀመረበት የመጀመሪያ ሰንበት ላይ የተነበበው ቅዱስ ወንጌል ኢየሱስ በምድረ በዳ የተፈተነበትን ሁኔታ ያቀርብልናል (ማር. 1፡12-15)። የመጽሐፍ ቅዱሱ ታሪክ “በምድረ በዳ በሰይጣን ተፈትኖ አርባ ቀን ኖረ” ይላል። እኛም በዐቢይ ጾም ወቅት “ወደ ምድረ በዳ እንድንገባ” ተጋብዘናል፣ ማለትም፣ ዝምታ፣ ውስጣዊው ዓለም፣ ልብን እንድንሰማ፣ ከእውነት ጋር እንድንገናኝ ተጋብዘናል። የዛሬው ቅዱስ ወንጌል በምድረ በዳ ውስጥ ክርስቶስ “ከአውሬዎች ጋር ነበረ” በማለት ተናግሯል። መላእክትም አገለግሉት” (ማርቆስ 1፡13)። የዱር አራዊት እና መላእክት የእርሱ ማህበርተኞች ነበሩ። ነገር ግን፣ በምሳሌያዊ አነጋገር፣ እነሱ የእኛም አጃቢዎች ናቸው፡ በእርግጥ፣ ወደ ውስጠኛው ምድረ በዳ ስንገባ፣ እዚያ የዱር አራዊትና መላእክትን እናገኛለን።

የዱር አራዊት! በምን መልኩ? በመንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ ልብን የሚከፋፍሉ፣ ውስጣቸውን ለመያዝ የሚሞክሩ እንደ ሥር የሰደዱ ስሜቶች ልንላቸው እንችላለን። እነሱ ያታልሉናል፣ አሳሳች ይመስላሉ፣ ካልተጠነቀቅን ግን እነርሱ ይበጣጥሱናል። ለነዚህ የነፍስ “አውሬዎች” ስም ልንሰጣቸው እንችላለን፡- የተለያዩ ምግባሮች፣ የሀብት መመኘት፣ በመተሳሰብና ባለመርካት ወደ እስር ቤት የሚያስገባን፣ የተድላ ከንቱነት፣ ዕረፍት ማጣትና ብቸኝነት የሚፈርጅ፣ ዝናን የመሻት ፍላጎት። አለመተማመንን እና ቀጣይነት ያለው የማረጋገጫ እና ታዋቂነት ፍላጎት የሚፈጥር - በውስጣችን ሊያጋጥሙን የሚችሉትን እነዚህን ነገሮች መዘንጋት የለብንም - ስግብግብነት ፣ ከንቱነት እና ራስ ወዳድነት። እንደ “ዱር” አውሬዎች ናቸው፣ እና እንደዚሁ መቃወም እና መታገል አለብን። ያለበለዚያ ነፃነታችንን አግበስብሰው ይወስዳሉ። እናም እነዚህን ነገሮች ለማስተካከል ወደ ውስጠኛው ምድረ በዳ እንድንገባ ይርዳን።

ከዚያም በምድረ በዳ መላእክት ነበሩ። እነዚህ የእግዚአብሔር መልእክተኞች ናቸው፣ የሚረዱን፣ በጎ የሚያደርጉልን ናቸው፡ በእርግጥም ባህሪያቸው፣ በወንጌል መሰረት፣ አገልግሎት ነው (ማርቆስ 1፡13)፣ ሀብት ከማካበት ጋር ፍፁም ተቃራኒ፣ የስሜታዊነት ዓይነተኛ ምልክቶች ናቸው። ሀብት ከማጋበስ በተቃራኒ የሚደረግ አገልግሎት። የመላእክት መንፈስ ይልቁንም በመንፈስ ቅዱስ የተጠቆሙትን መልካም ሀሳቦች እና ስሜቶች ያስታውሳሉ። ፈተናዎች ሲለያዩን፣ መልካም ነገሮች መለኮታዊ መነሳሻዎች አንድ ያደርጉናል እና ወደ ስምምነት እንግባ፡ ልብን ያረካሉ፣ የክርስቶስን ጣዕም፣ “የገነትን ጣዕም” ያጎናጽፋሉ። እናም የእግዚአብሔርን መነሳሳት ለመረዳት አንድ ሰው ወደ ጸጥታ እና ጸሎት መግባት አለበት። የዐብይ ጾም ጊዜ ደግሞ ይህን ለማድረግ ነው የሚጠቅመን።

ራሳችንን ልንጠይቅ እንችላለን፣ በመጀመሪያ፣ በልቤ ውስጥ የሚቀሰቅሱት የተዘበራረቁ ስሜቶች፣ “አውሬዎች” ምንድን ናቸው? ሁለተኛ ጥያቄ፡ የእግዚአብሔር ድምፅ ለልቤ እንዲናገር እና በመልካምነት እንዲጠብቀው ለመፍቀድ፣ ወደ “ምድረ በዳ” ትንሽ ለማፈግፈግ እያሰብኩ ነው፣ በዚህ ቀን ቦታን ለመስጠት እየሞከርኩ ነው?

ቃሉን የጠበቀች ለክፉው ፈተና እራሷን ያላስደፈረችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዐብይ ጾም ጉዟችን መልካም ነገር እንድናደርግ እርሷ ትርዳን።

23 March 2024, 14:34