ፈልግ

በህንድ ፥ ማኒፑር በተቀሰቀሰው ግጭት መኪና ሲቃጠል። በህንድ ፥ ማኒፑር በተቀሰቀሰው ግጭት መኪና ሲቃጠል።  (AFP or licensors)

የህንድ ግዛት በሆነችው ማኒፑር በተከሰተ የሃይማኖት ግጭት ምክንያት በክርስቲያኖች ላይ የሚደርሰው ስደት አሳስቦኛል አሉ የህንድ ሊቀ ጳጳስ

የባንጋሎር ሊቀ ጳጳስ የሆኑት ፒተር ማቻዶ በህንድ ማኒፑር ግዛት ዉስጥ በሚኖሩ ክርስቲያኖች ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት እና ቤታቸውን በእሳት የመቃጠሉ ድርጊት እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል።

የዚህ ዜና አዘጋጅ ዘላለም ኃይሉ - አዲስ አበባ

የባንጋሎር የሜትሮፖሊታን ሊቀ ጳጳስ አርብ ዕለት ባወጣው መግለጫ በማኒፑር ግዛት ውስጥ ብጥብጥ ከተነሳ በኋላ ክርስቲያኖችን ኢላማ ያደረገው ሃይማኖታዊ ጥቃት እና ስደት አሳሳቢ እንደሆነ አውስቷል።

ሊቀ ጳጳስ ፒተር ማቻዶ እንዳሉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በክልሉ በክርስቲያኖች ላይ የሚደርሰው ትንኮሳ እያገረሸ መምጣቱን ነው አትኩሮት ሰጥተው የተናገሩት።

"... 1974 የተገነቡ ሶስት አብያተ ክርስቲያናት እና አንዳንድ መኖሪያ ቤቶች እንደተቃጠሉ እንደዚሁም ህዝቡ ወደ ተሻለ ሠላም ያለበት ቦታዎች ለመሰደድ እንደተገደዱ ሪፖርቶች ደርሰውናል" ብለዋል።

በተጨማሪም 12 በላይ አብያተ ክርስቲያናት መቃጠላቸውን በብዙዎቹም ላይ እርኩሰት እንደደረሰባቸው እና እንዲሁም የካቶሊክ ቤተክርስቲያን የኢየሱሳውያን ማህበር ካህናት ላይ ማስፈራሪያ እና ዛቻ እንደደረሰባቸው የሚገልጹ ዘገባዎችም ወጥተዋል።

ሊቀ ጳጳሱ አክለውምይህ የሚያሳየው በሃይማኖታዊ አመለካከት እና ልማዳቸው ኢላማ በሚደረግባቸው ሰዎች ላይ የሚደርሰውን አደጋ አሳሳቢ መሆኑን ነውብለዋል።

"ሁኔታው በቁጥጥር ስር እንደሚውል ተስፋ እናደርጋለን ለዚህም አበክረን እንጸልያለን ለማኒፑር ህዝብ ሠላም እና በራስ መተማመን ይመለሳል" ብለዋል።

ሊቀ ጳጳሱ እንዳሉት የሃይማኖት ነፃነትን ማረጋገጥ የመንግስት ሃላፊነት እንደሆነ እና በተለይ ደግሞ ህዝቡ በስልጣን ላይ ላለው ፓርቲ አደራ መስጠቱን ጠቁመዋል።

 የማኒፑሩ ግጭት

 በማኒፑር ውስጥ ያለው ብጥብጥ የተነሳው እሮብ እለት በተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ሲሆን ይህም በአብዛኛው ሂንዱዎች እና ሙስሊሞች ባቀፈው የሜቴይ ጎሳ ማህበረሰብ እና ባብዛኛው ክርስቲያን በሆኑ ናጋ ጎሳ መካከል ውጥረቱ እየጨመረ በመምጣቱ ነው።

በሁከቱ መሃል ወደ 9,000 የሚጠጉ ሰዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል ነገር ግን በትክክል የጠፋው የሰው ህይወት ቁጥር እና የንብረት ውድመት እስካሁን አልተገለጸም።

የጠቡ ምንጭ የተባለዉም ባለፈው የሜይቲ ጎሳዎች ከስራ እና ከመሬት መብቶች አንፃር የተወሰኑ ጥቅማጥቅሞችን የሚያረጋግጥላቸው እና እውቅና እንዲሰጠው ያቀረቡት ጥያቄ በመቃወም ነው የሜይቲ ጎሳ ያልሆኑት ቡድኖች ብጥብጡን ያስነሱት ተብሏል።

በማኒፑር ውስጥ 50% በላይ ህዝብ የሜይቲ ጎሳ አባል እንደሆነም ተዘግቧል።

08 May 2023, 12:44