ፈልግ

ዓለም አቀፍ የሰራተኞች ቀንን በማስመልከት በማኒላ ከተማ የተደረገ ሰልፍ ዓለም አቀፍ የሰራተኞች ቀንን በማስመልከት በማኒላ ከተማ የተደረገ ሰልፍ   (AFP or licensors)

የፊሊፒንስ ጳጳስ፡ በፊሊፒንስ ውስጥ ያለው መሠረታዊ ደመወዝ 'ፍትሃዊ ያልሆነ' ነው አሉ።

በፊሊፒንስ የዋጋ ጭማሪ ሲኖር ዝቅተኛው የደመወዝ መጠን ላይ ጭማሪ ለማድረግ የሚያስችል ሕግ እንዲወጣ አንድ የፊሊፒንስ ጳጳስ ጥሪ አድርገዋል። ጳጳሱ በማከልም አሁን እየተከፈለ ያለው መሠረታዊ ደመወዝ ለኑሮ በቂ አይደለም ብለዋል።

  ዘላለም ኃይሉ ፥ አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

የሳን ካርሎስ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጄራርዶ አልሚናዛ የፊሊፒንስ ሠራተኞችን ሁኔታ በቁጭት ገልጸው የዋጋ ግሽበ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየቀነሰ ቢመጣም በሀገሪቱ የሸቀጦች ዋጋ ጨምሮ በነበረበት ዋጋ ቀጥሏል ሲሉ ተናግረዋል።

ጳጳሱ ማክሰኞ ከቫቲካን ዜና ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ በፊሊፒንስዝቅተኛ ደመወዝብለን የምንጠራው ፍትሃዊ ደሞዝ ወይም የሚያኖር ደሞዝ ወይም ለቤተሰብ የሚሆን ደሞዝ አይደለም ብለዋል።

 

የፊሊፒንስ ብሄራዊ ደሞዝ እና ምርታማነት ኮሚሽን መረጃ እንደሚያሳየው በሃገሪቱ ለአንድ ሰው የሚከፈለው አማካይ ወራዊ ደሞዝ 8,902 ፔሶ ሲሆን ይህም ወደ ዩሮ ሲቀየር 145 ዩሮ መሆኑ ነው።

በአንፃሩ የፊሊፒንስ ስታትስቲክስ ባለስልጣን ... 2021 እንደዘገበው አምስት ሰዎች ላለው የቤተሰ አባላት መሠረታዊ የምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ መስፈርቶችን ለማሟላት የሚያስፈልገው አነስተኛ ወርሃዊ ገቢ 12,030 ፔሶ (196.45 ዩሮ) ነው። ይህ ማለት ግን እያንዳንዱ የቤተሰብ አባል በቀን 80 ፔሶ (1.31 ዩሮ) መኖር አለበት ማለት ነው።

 እየተባባሰ ያለው ችግር

የሸቀጦች ዋጋ በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱ ፊሊፒናውያን የደመወዛቸው ትክክለኛ ዋጋ እየቀነሰ ስለሚሄድ አንድን ነገር መክፈል በሚችሉት አቅም ለማግኘት አዳጋች ሆኖባቸዋል።

ጳጳሱ አክለውም በሀገሪቱ ውስጥ እየተከፈለ ያለው ደሞዝ ከዋጋ ጭማሪው ጋር አልተዛመዱም ብለዋል

 

አብዛኞቹ ሠራተኞች ለድህነት ተዳርገዋል ስለዚህ ባለፉት ዓመታት የሰራተኞች ሁኔታ እንዴት ነው ብለህ ብትጠይቀኝ በእርግጥም ተባብሷልሲሉም አክለዋል።

 

ጳጳሱ በቂ ካልሆነው ዝቅተኛ ክፍያ በተጨማሪ አንዳንድ ሰራተኞች ጥቅማ ጥቅሞች እና የቆይታ ጊዜ ዋስትና እንደሌላቸው ተናግረዋል።

 

በተጨማሪምየቤተክርስቲያን ሰዎች የሠራተኞች ህብረት’ (CWS) ሊቀመንበር የሆኑት ጳጳስ አልሚናዛ በፊሊፒንስ የግብርና ዘርፍ ላይ የተሰማራው እና ምግብ የሚያመርተው የህብረተሰብ ክፍል ከደሃውም እጅግ የከፋ ደሃ መሆኑን ጠቁመዋል።

 

ኤጲስ ቆጶሱ እንደተናገሩት በሀገሪቱ ውስጥ የደመወዝ ጭማሪን ለማድረግ ሃሳብ ላላቸው ሁለት የኮንግረስ ሰነዶች ማህበሩ (CWS) ድጋፉን አሳይቷል። እነዚህም 750 ፔሶ የዝቅተኛ ደመወዝ ላይ ጭማሪ ለማድረግ ሀሳብ ያለውየቤት ሰነድ ቁጥር 7568’ የሚባለው እናየሴኔት ሰነድ ቁጥር 2002’ የተባለው 150 ፔሶ ጭማሪ ለማድረግ ጥረት የሚያደርገው እንደሆነም ታውቋል።

 

ለሠራተኞቹ የሚገባቸውን መስጠት አለብን ፍትህን ለመስጠት ይህ የልግስና እና የፍቅር መሰረታዊ መስፈርት ነውሲሉ ጳጳሱ ተናግረዋል።

 

የፍራቴሊ ቱቲ 'Fratelli tutti' ጽንሰ ሃሳብ በደመወዝ ላይ

ጳጳሱ በሰጡት መግለጫ ደመወዝአስፈላጊ እና ፍትሐዊእንደሆነና እንዲሁም ለካቶሊክ ቤተክርስቲያን አስተምርሆም መሠረታዊ ነገር ነው ምክንያቱም ከሰው ልጅ ክብር ጋር የተቆራኘ ነውናብለዋል።

 

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደገው የአናጺ ልጅ ሆኖ ነበር እሱ የአናጢው ልጅ ተብሎ ተጠርቷል ስለዚህም ለሥራ የሚሰጠውን ክብርን ያመጣው ኢየሱስ ነበርበማለት በመንፈሳዊ ጎኑ ያለውን እምድምታ አብራርተዋል።

ጳጳሱ አክለውምየቤተ ክርስቲያን ማኅበራዊ ትምህርት የሠራተኞችን ክብር ማስጠበቅ ነውብለዋል።

 

ነገር ግን ኤጲስ ቆጶስ አልሚናዛ እንዳሉት በደመወዝ እና በጉልበት ሠራተኛው ላይ ያሏቸው አቋም አጠቃላይ መሠረት ያደረገው የርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቺስኮስ ኢንሳይክሊካል ራቴሊ ቱቲ (ሁላችንም ወንድማማቾች ነን እንደማለት ነው) ላይ እንደሆነ በመግለጽእኛ ወንድማማቾች እና እህትማማቾች ነን ስለሆነም በቤተሰብ ውስጥ ከሆንን በቤተሰቡ ዉስጥ ያለዉን ማንኛውንም ነገር እንካፈላለን እርስ በርሳችን እንረዳዳለን እንጠብቃለን ነገር ግን ይህ በሥራ ቦታ እየሆነ አይደለምብለዋል።

 

የፊሊፒንስ ሰራተኞች እንክብካቤ እንደማይደረግላቸው እና ብዙ ጊዜ በደካማ እና ጨቋኝ ሁኔታዎች ውስጥ እንደሚሰሩም አክለዋል። በመቀጠልም ኩባንያዎች ሰራተኞቻቸውን እንደ ቤተሰብ እንዲያስቡ ጥሪ አቅርበዋል ምክንያቱም ደግሞ ይላሉየጉልበት ሠራተኛ የሌለበት ኢኮኖሚ በጭራሽ አያድግምሲሉ ጳጳሱ ተናግረዋል።

 

ከዚህ ቀደም በርካታ ቡድኖች በፊሊፒንስ የደመወዝ ጭማሪ እንዲደረግ ጠይቀዋል ሆኖም ... 1986 ጀምሮ ከነበሩት ስድስት አስተዳደሮች መካከል ዝቅተኛ የደመወዝ ጭማሪ የተደረገው በቀድሞው ፕሬዝዳንት ሮድሪጎ ዱቴርቴ አስተዳደር ሲሆን ይህም 2016 እስከ 2022 በነበረው ዝቅተኛ ደመወዝ ላይ 16.1 በመቶ ጭማሪ ብቻ ነበር።

 

ይህ በእንዲህ እንዳለ አሁን በስልጣን ላይ ያሉት ፕሬዝዳንት ፈርዲናንድ ማርኮስ ጁኒየር ምንም አይነት የደመወዝ ጭማሪ እንዳልፈቀዱ ታውቋል።

10 May 2023, 12:28