ፈልግ

እ.አ.አ ግንቦት 10 ቀን 1973 ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቅዱስ ጳውሎስ ስድስተኛ እና ጳጳስ ሺኑዳ ሳልሳዊ በቫቲካን እ.አ.አ ግንቦት 10 ቀን 1973 ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቅዱስ ጳውሎስ ስድስተኛ እና ጳጳስ ሺኑዳ ሳልሳዊ በቫቲካን  

የኮፕቲክ ቤተክርስቲያን ክርስቲያኖች 'በዋጋ የማይገመት' ትዉፊቶችን አቆይተውልናል ተባለ።

በኔዘርላንድስ የግሮኒንገን ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ተማሪ የሆኑት አልቤርቶ አልፍሬዶ ዊንተርበርግ በስነ መለኮት እና ሃይማኖታዊ ጥናቶች ፋኩልቲ ውስጥ የጥንቱን የኮፕቲክ ክርስቲያኖች ልምድ እና ወግ ይዳስሳሉ።

ዘላለም ኃይሉ አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ባህላዊ እና ታሪካዊ ጠቀሜታ ያለው የማይለካ ውድ ሀብት ይዛ ትገኛለችሲሉ በኔዘርላንድ ውስጥ በግሮኒንገን ዩኒቨርሲቲ የቲኦሎጂ እና የሃይማኖት ጥናቶች ፋኩልቲ ውስጥ የዶክትሬት ተማሪ የሆኑት አልቤርቶ አልፍሬዶ ዊንተርበርግ ተናግረዋል።

የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ፓትርያርክ ታዎድሮስ 2 በቫቲካን የሚያደርጉትን ጉብኝት አስቀድሞ አቶ ዊንተርበርግ የቫቲካን ዜና ባልደረባ ከሆኑት ቶማስ ማቲካ ጋር በግብፅ የነበሩት እና አሁንም ድረስ ስላሉት ጥንታዊ ክርስቲያኖች ወግ እና ባህል ተነጋግረዋል።

 

ኮፕቲኮች ከጥንት ጀምሮ ከፈርዖናዊ ግብፃውያን የዘር ሃረግ የሚመዘዝ እና ሥር መሰረታቸው የግብፅ ተወላጅ የሆኑ አናሳ ቁጥር ያላቸው ክርስቲያኖች ናቸውሲል ገልጿል።

 በቅዱስ ማርቆስ የተመሰረተ

የኮፕቲክ ክርስትያኖች አናሳ ቁጥር ያላቸው ሲሆኑ ከጠቅላላው የግብፅ ህዝብ ብዛት ከስምንት እስከ አስር በመቶው ይደርሳሉ አብዛኛዎቹ የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አባል ናቸው እንደ ትውፊት ፥መነሻውን የቅዱስ ጴጥሮስ ደቀ መዝሙር በሆነው በወንጌላዊው በቅዱስ ማርቆስ የተመሰረተ የአሌክሳንደሪያው ቅድስት መንበር እምነት ነው።

አቶ ዊንተርበርግ እንደሚገልፁት ልዩ የሆነ የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ምስረታ451 ከተካሄደው የኬልቄዶን ጉባኤ ማግስት የተከናወነ ረጅም ሂደት ነበርሲሉ ያስረዳሉ። ምንም እንኳን በጉባኤው ላይ የተከሰቱት አለመግባባቶች ምክንያት ግንባር ቀደም የሆነው የክርስቶሎጂ ወይንም ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጥያቄዎች ቢሆኑም አቶ ዊንተርበርግ እንደሚሉት በአሌክሳንድሪያ ቤተክርስቲያን እና በሮማ ቤተክርስቲያን መካከል ያለው ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ከፍተኛ ሚና መጫወታቸውን ይጠቅሳሉ።

 

ግብፅ ከሁለት መቶ ዓመታት በኋላ በእስላማዊ ኃይሎች በተወረረች ጊዜ የግብፅ ክርስቲያኖች ወይ እስልምናን እንዲቀበሉ ወይም ከባድ ግብር እንዲከፍሉ ተገደዱ።በረጅም የኢኮኖሚ ገደቦች ህዝቡን በማዋረድ ሃይማኖታዊ ይዘት ነበረው ግድያ እና በወራሪዎቹ ገዥዎች በኮፕቲኮች ላይ በደረሰው ኃይለኛ ስደት ምክንያት የቀድሞ የክርስትና እምነት ተከታዮች ወደ አናሳነት ተቀይረዋል። ይሁን እንጂ እስከ ዛሬ ድረስ በሕይወት ተርፈዋል።

 የሰማዕታት ቤተ ክርስቲያን

አቶ ዊንተርበርግ የኮፕቲክ ክርስትና ለሰፊው ቤተ ክርስቲያን ያበረከተውን አስተዋፅዖ ሲያብራሩ በመጀመሪያ ላይ የሚያስቀምጡት ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን የገዳማዊነት ተቋም መሆኗን ነው ይህም ከጥንቷ ሶርያ ጋርም የተያያዘ ነው ይላሉ። የምዕራባውያን ምንኩስናን መስራች በሆነ በቅድስት ቤነዲክ ላይ ጠቃሚ ተጽእኖዎችን ያሳደሩትን የኮፕቲክ ቅዱሳን የሆኑትን የበረሃው አባቶች መካከል በተለይም ታላቁ ቅዱስ እንጦንዮስ እና ቅዱስ ፓኮሚየስን ማስታወስ አስፈላጊ እንደሆነ ይጠቅሳሉ።

 

አቶ ዊንተርበርግ በጥንቷ ቤተክርስቲያን በግብፃውያን ክርስቲያኖች ላይ የደረሰውን የስደት ታሪክ አስታውሰዋል።ከኮፕቲክ መነኮሳት እና መናኞች ታላቅ ታሪክ በተጨማሪ የሮማ ግዛት በነበረችው ግብፅ በንጉሠ ነገሥት ዲዮቅልጥያኖስ ዘመን በክርስቲያኖች ላይ በደረሰው እንግልት እና ስደት በጣም ከተጎዱት መካከል አንዱ ነውብለዋል።በመሆኑም የኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን የራሷ የቀን አቆጣጠር በአፄ ዲዮቅልጥያኖስ ዘመነ መንግስት 284 .. የጀመረች እና ራሷን እንደ ሰማዕት ቤተክርስቲያን ትገልጻለች ብለዋል።

ክርስቲያናዊ እና ሥነ-መለኮታዊ ውይይት

በአሁኑ ጊዜ የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የአሌክሳንድርያ ፓትርያርክ በሆኑት ሊቀ ጳጳስ ታዎድሮስ ዳግማዊ የሚመራ ሲሆን በስሯም ወደ አሥር ሚሊዮን የሚጠጉ ምእመናን አሏት። ከግብፅ እና ከመካከለኛው ምስራቅ በተጨማሪ በአሜሪካ በካናዳ በአውስትራሊያ በፈረንሳይ እና በጀርመን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የኦርቶዶክስ ኮፕቲኮች ይገኛሉ።

 

50 ዓመታት በፊት .. ግንቦት 10 ቀን 1973 ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ቅዱስ ጳውሎስ ስድስተኛ እና ጳጳስ ሺኑዳ ሳልሳዊ በቫቲካን ተገናኝተው በነበረበት ወቅት ታሪካዊየክርስቲያናዊ የጋራ ሰነድJoint Christological Declaration የተባለውን ሰነድ ፈርመዋል። መግለጫው ወይም ሰነዱ ሁለተኛው የቫቲካን ጉባኤን ተከትሎ በካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እና በኮፕቲክ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት መካከል ለዓመታት ሲካሄድ የቆየው የክርስትና እና ሥነ-መለኮታዊ ውይይት ተከትሎ ነበር።

11 May 2023, 13:14