ፈልግ

ፍልስጤማውያን የናክባ 75ኛ ዓመት በራማላህ ሲያከብሩ ፍልስጤማውያን የናክባ 75ኛ ዓመት በራማላህ ሲያከብሩ  

በቅድስት ሀገር ያሉ የቤተክርስቲያን መሪዎች ፍትሃዊ ሠላም እንዲሰፍን ተማጽነዋል

በእየሩሳሌም የሚገኙት ሊቀ ጳጳሳት እና የሃይማኖት መሪዎች ፥ የፍልስጤም የአል ናክባን መታሰቢያ በዓል ማዕከል ባደረገው መግለጫ ፥ በሀገሪቷ ዓለም አቀፍ ህግን መሰረት ያደረገ ዘላቂ እና ፍትሃዊ ሠላም እንዲሰፍን እና ለቅዱሳን ስፍራዎች ክብር እንዲሰጥ ጥሪያቸውን በድጋሚ አቅርበዋል።

አዘጋጅ ዘላለም ኃይሉ አዲስ አበባ

ፍልስጤማውያን የአል-ናክባ (የጥፋት አደጋ) 75 ዓመትን ሲያከብሩ ... 1948 የእስራኤል መንግሥት እንደ ሃገር በተፈጠረበት ቀን ከትውልድ አገራቸው በግዳጅ የተባረሩበትን ቀን በማሰብ በኢየሩሳሌም የሚገኘው የሃይማኖት አባቶች እና የአብያተ ክርስቲያናት ሓላፊዎች በቅድስት ሀገር ፍትሐዊና ዘላቂ ሠላም እንዲሰፍን የአብያተ ክርስቲያናትን ጥሪ በድጋሚ ገልፀዋል።

 መከባበር ሠላምን ለማስፈን አንዱ መንገድ ነው።

እምነታችን የሚያስተምረን ሁላችንም እንደ ሰው ልጅ ወንድማማቾች እና እህቶች መሆናችንን እና ሠላምን መቻቻልን እና ፍትህን ለማስፈን ተባብረን መስራት እንዳለብን ነውሲል ሰኞ ዕለት የተለቀቀው መግለጫ አስነብቧል። መግለጫው በማከልምፍቅር ርህራሄ እና መከባበር በዓለም ላይ ሠላምን የምናመጣበት መንገድ መሆናቸውን ክርስትና አስተምሮናል እናም ይህ በተለይ ለተወዳጅዋ ቅድስት ሀገራችን ተግባራዊ መሆን አለበትይላል።

ናክባ ... 1948 700,000 በላይ ፍልስጤማውያን የተሰደዱበትን ወይም ከቤታቸው የተፈናቀሉበትን ወቅት ያስታውሳል።   የእነዚህ በመካከለኛው ምስራቅ 5 ሚሊዮን በላይ የሚገመቱት ስደተኞች እና የዘሮቻቸው እጣ ፈንታ በመካሄድ ላይ ባለው የአረብ-እስራኤል ግጭት ውስጥ ትልቅ አከራካሪ ጉዳይ ሆኖ ቀጥሏል።  እስራኤል እነዚህ ስደተኞች በጅምላ ቅድመ አያቶቻቸው ከረጅም ጊዜ በፊት ሲኖሩባቸው ወደ ነበሩበት ቤቶች ወይም አከባቢዎች እንዲመለሱ የቀረበላትን ጥያቄ ውድቅ አድርጋለች።

 ያገረሸው የእስራኤል እና የፍልስጤም ጥቃት

በዚህ ዓመቱ ክብረ በዓል የሚከበረው ከጥር ወር ጀምሮ 140 በላይ ፍልስጤማውያን እና ቢያንስ 19 እስራኤላውያን እንዲሁም የውጭ ዜጎች የሞቱበት የእስራኤል እና የፍልስጤም ብጥብጥ ዳራ ላይ ነው።

በእስራኤል ፍልስጤማዊያን በሚታሰሩበት እስር ቤት ውስጥ እስረኞቹ ባደረጉት የረሃብ አድማ ምክንያት በሞቱት ፍልስጤማዊያን ሰበብ በግንቦት ወር የመጀመሪያ ሳምንት ጀምሮ ብጥብጡ ተባብሷል። በዚህም የተነሳ የፍልስጤም እስላማዊ ጂሃድ (በጋዛ ሰርጥ ከሃማስ ቀጥሎ ሁለተኛው ትልቁ ታጣቂ ቡድን) እና ሌሎች ቡድኖች በሁለት ቀናት ውስጥ ብቻ 100 በላይ ሮኬቶችን ወደ እስራኤል ተኩሰዋል። ይህም የሮኬት ጥቃት የተደረገው እስራኤል በሃማስ እና ኢስላሚክ ጂሃድ ኢላማዎች ላይ የፈጸመችውን ገዳይ የአየር ጥቃት ተከትሎ ነው።

... ከነሐሴ 2022 ወዲህ በእስራኤል ኃይሎች እና በፍልስጤም ታጣቂዎች መካከል ከፍተኛው የተባለ ጦርነት ባለፈው ሳምንት ተካሂዷል።

የሰብአዊ መብቶች እና የዓለም አቀፍ ህጎች መከበር

የኢየሩሳሌም ፓትርያርኮች በመግለጫቸውሠላም የሚረጋገጠው በፍትሃዊነት የሰብአዊ መብቶች እና የዓለም አቀፍ ህጎች ሲከበሩ ብቻ ነውብለውሁሉም ሰው የተሻለ እና የበለጠ ሰብአዊነት ያለው የወደፊት ህይወት ለመገንባት በጋራ እንዲሰራበድጋሚ አሳስበዋል።

ፍትህ እና ሠላም ለቀጣናው መረጋጋት እና ብልጽግና ቁልፍ ሚና አላቸው ብለን እናምናለን እናም እነዚህን መልካም ግቦች ለማሳካት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆናችንን እንገልፃለን

ለቅዱስ ቦታዎች እና ለነባራዊ ሁኔታዎች ክብር መስጠት

መግለጫው በቅርቡ በእስራኤል ጽንፈኞች በአብያተ ክርስቲያናት ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት እና በክርስቲያኖች ላይ የሚደርሰውን አካላዊ እና ሞራላዊ ጥቃት በተዘዋዋሪ በመጥቀስ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማህበረሰቦች የሚደረገውን ጥበቃ በመደገፍ እና ቅዱሳን ቦታዎችን እንዲሁም አሁን ላይ ያለውን ነባራዊ ሁኔታን በመጠበቅ ረገድ የላቀ ሚና እንዲጫወት ጠይቋል።

የቤተ ክርስቲያን መሪዎቹ እግዚአብሔር ለፍልስጤም ህዝብ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን የሃገረ መንግስት ግንባታ እና የብልጽግና መብት እንዲሰጣቸው እንዲሁም በቅድስት ሀገር ውስጥ ያሉ ህዝቦች በሙሉ በሠላም በክብር እና በብልጽግና መኖር እንዲችሉ በመጸለይ ተጠናቋል።

17 May 2023, 10:57