ፈልግ

የኩባው ካሪታስ አባላት በሥራ ላይ የኩባው ካሪታስ አባላት በሥራ ላይ  (Caritas Cuba)

የካሪታስ ዋና ተግዳሮቶች 'በዓለም ላይ በጣም ድሃ የሆኑ ሰዎችን መድረስ ነው

የዓለም አቀፉ የካሪታስ ጠቅላላ ጉባኤ ልዑካን ኪርስቲ ሮበርትሰንን እንደ አዲስ ምክትል ፕሬዘዳንትነት እንደመረጡ ፥ ወይዘሮዋ በሚቀጥለው የሥራ ጊዜያቸው የቤተክርስቲያኒቷን የሰብአዊ ኮንፌዴሬሽን ተልዕኮን ለማደስ ያላቸውን ተስፋ ገልፀዋል።

ዘላለም ኃይሉ አዲስ አበባ

22ኛው የካሪታስ ዓለም አቀፍ ጠቅላላ ጉባኤ በሮም እየተካሄደ ሲሆን አዲስ የተመረጡት ፕሬዝዳንት እና ዋና ፀሀፊ ለዓለም አቀፉ ኮንፌዴሬሽን ቀጣይ ጉዞ የሚመሩበትን ስልታዊ ዕቅድ ጋዜጣዊ መግለጫ በማዘጋጀት ጉባኤውን ማክሰኞ ዕለት ሊያጠናቅቁ ዕቅድ ተይዟል።

ሰኞ ዕለት ልዑካኑ ኪርስቲ ሮበርትሰንን የዓለም አቀፉ ካሪታስ ምክትል ፕሬዝዳንት አድርገው መርጠዋል። ክርስቲ ... 2019 ጀምሮ የካሪታስ አውስትራሊያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነው አገልግለዋል ከዚህ ቀደም በካሪታስ አውስትራሊያ የፓሲፊክ ፕሮግራሞች አስተባባሪ እና የግንኙነት ቡድን መሪነትን ጨምሮ የተለያዩ የሥራ ቦታዎች ላይ ሠርተዋል።

ሮበርትሰን ለቫቲካን ዜና እንደተናገሩት በዓለማችን 160 በላይ ሀገራት የተውጣጡ የካሪታስ ቤተሰብ አባላትየወንድማማችነት አዲስ ጎዳና መገንባትበሚል መሪ ቃል አንድ ላይ ተሰባስበዋል።

 “ወደዚህ ስብሰባ የመጣነው የእርስ በእርስ ግንኙነቶችን ለመገንባት እና ለማጠናከር ሲሆን ነገር ግን ራሳችንን በአዲስ አካሄድ ገንብተን ለኮንፌዴሬሽኑ አዲስ መንገድ ለማዘጋጀት መሆኑንም ጭምር በመረዳት ነውብለዋል።6 ቀናት ስብሰባ ላይ ሁሉም ተሳታፊዎች እንደ ኮንፌዴሬሽን አዲስ የቀጣይ መንገድ አቅጣጫ ለመንደፍ ፈቃደኞች እንደሆኑ ግልጽ ነውበማለት አክለውበታል።

  “የዓለም አቀፍ ካሪታስ አባል የሆኑ162 ሃገር አቀፍ የካሪታስ አባል ድርጅቶችን ያቀፈው እና በሰብአዊ ሥራ ላይ በአስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ ላይ እና በዘላቂ ዕርዳታ ላይ የተሰማራውየቤተ ክርስቲያን የእርዳታ እጆችበመባል የሚታወቀው ዓለም አቀፍ ካሪታስ ትሥሥር ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቺስኮስ ባለፈው ህዳር ጊዜያዊ አስተዳደር ከሾሙለት በኋላ አሁን ላይ ጥልቅ ተሃድሶ ላይ እንዳለም አዲስ ተመራጯ ወይዘሮ ክርስቲ ገልፀዋል።

ወይዘሮዋ እሁድ ዕለት ካሪታስ ኢንተርናሽናልስ የሚሰራውንየተልእኮውን የጋራ እሴትለማጉላት የድርጅቱ አዲስ ስትራቴጂያዊ ማዕቀፍ መጀመሩን ጠቁመዋል።

ሁሉም አባሎቻችን ወንድማማችነትን ለመገንባት እና በዓለም ላይ ያሉ እጅግ በጣም ድሃ ህዝቦችን ለማገልገል አዳዲስ መንገዶችን በመፈለግ በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ ናቸውሲሉም ተናግረዋል።

 

አዳዲስ ተግዳሮቶች

አዲሷን የካሪታስ ምክትል ፕሬዝዳንት ወደፊት በሚመጣው የሥራ መንገድ ላይ ዋና ዋና ፈተናዎች ሆነው ምን እንደሚጠብቃቸው ተጠይቀው እንደተለመደው ዓለም አቀፉን ካሪታስ የሚያጋጥሟቸው ተግዳሮቶች የዓለም ድሃ ህዝቦችን የሚያጋጥሟቸው ፈተናዎች ናቸውብለዋል።

በአሁኑ ወቅት በዩክሬን በመካከለኛው ምስራቅ ክፍሎች እና በአፍጋኒስታን እየተደረጉ ያሉ ግጭቶችና እና እንዲሁም በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በተከሰቱ ተግዳሮቶች በኦሽንያ እና በአፍሪካ ውስጥ የምናገለግላቸውን ማህበረሰቦች ምን ያህል እየተጎዱ እንዳሉ እያየን ነውሲሉም ተናግረዋል።   

የዓለም አቀፉ ካሪታስ ፈተናዎች የግድ የእኛ ፈተናዎች ሊሆኑ አይችሉም

ወይዘሮ ሮበርትሰን በመቀጠልእንደ ድርጅት ትኩረታችንን ዛሬ በምናገለግላቸው ሰዎች ላይ ማድረግ እንፈልጋለን ብለዋል።

አዲስ ስለተመረጡት ፕሬዝዳንት መደሰታቸው

ኪርስቲ ሮበርትሰን ሊቀ ጳጳስ ታርሲየስ ኪኩቺ እንደ አዲሱ የካሪታስ ኢንተርናሽናል ፕሬዝደንት ሆነው በመመረጣቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው የምርጫው ሂደቱ እጅግ ንፁህ ግልጽ እና ፍትሃዊ እንደነበር ተናግረዋል። በማከልምየኮንፌዴሬሽኑ አባላት ተስፋ አድርገውት የነበረው ይህንኑ ነበርብለዋል።

የቶኪዮ ሊቀ ጳጳስ የዓለም አቀፍ ካሪታስ ፕሬዝደንት ሆነው በተመረጡበት ወቅት ልዑካኑ ድጋፋቸውን ገልጸዋል ይህም ከሁሉም የካሪታስ አባላት ያላቸውን ድጋፍ አጉልቶ አሳይቷልበማለት ሃሳባቸውን ደምድመዋል።

16 May 2023, 12:54