ፈልግ

በመንፈስ ቅዱስ ያለን እምነት በመንፈስ ቅዱስ ያለን እምነት 

በመንፈስ ቅዱስ ያለን እምነት

የእምነት ቀዳሚ ምሥጢር በሆነው ጥምቀታችን ኃይል መሠረትነት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለው መንፈስ ቅዱስ ከአብ መንጭቶ በወልድ አማካይነት ስለተሰጠን ሕይወት በጥልቀትና በግል ይገልጽልናል፡፡ በጸጋው አማካይነት እምነትን በውስጣችን በማስጀመር አዲሱን ሕይወት ለእኛ በማስተላለፍ ረገድ መንፈስ ቅዱስ ግምባር ቀደም ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ማመን፣ መንፈስ ቅዱስ ከቅድስት ሥላሴ አካላት አንዱ መሆኑን ከአብና ከወልድም ጋር አንድ ህልውና ያለው መሆኑን ማመን ነው፡፡ እርሱ «አብና ከወልድ ጋር አብሮ ይሰገድለታል፤ ይከብራልም፡፡» የደኅንነታችን እቅድ ተጀምሮ ፍጻሜ እስከሚያገኝ ድረስ መንፈስ ቅዱስ ከአብና ከወልድ ጋር አብሮ ይሠራል፡፡ አብ ወደ ልባችን የላከው፣ መንፈስ፣ በእውነት አምላክ ነው (ገላ.4፡6)፡፡ ከአብና ከወልድ ጋር ህልውናው አንድ በመሆኑ መንፈስ ቅዱስ በሥላሴ ውስጣዊ ሕይወትና ለዓለም ባበረከተው ፍቅር ጭምር ከእነርሱ ፈጽሞ አይለይም፡፡ አብ ቃሉን በሚልክበት ጊዜ እስትንፋሱንም ሁልጊዜ ይልካል፡፡ በጋራ ተልእኮአቸው ወልድና መንፈስ ቅዱስ የተለዩ ቢሆኑም አይነጣጠሉም፤ እርግጠኛ ለመሆን የማይታየው እግዚአብሔር ገሀድ ተምሳሌት ክርስቶስ ቢሆንም፣ የሚገልጠው ግን መንፈስ ቅዱስ ነው (ት/ክርስቶስ፤ 208-209) ፡፡ ይህ የጌታ መንፈስ በእያንዳንዳችን ላይ የቤተ ክርስቲያን ምሥጢራት በምንቀበልበት ጊዜ ያርፋል፡፡ ይህ አንዱ መንፈስ እንደየ ስጦታችን እግዚአብሔርን እንድናገለግል ያነሣሣናል፤ ያው አንዱ የጌታ መንፈስ እንደምመራን እስከ ዕለተ ሞታችን በእግዚአብሔር ፊት እንመላለሳለን፡፡ እግዚአብሔር ዛሬ በውስጣችን አድሮ የሚሠራው በመንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ ይህ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ኃይልና ሙላት እንደሆነ እናምለን፡፡

05 August 2020, 12:13