የር. ሊ. ጳ ፍራንችስኮስ የምርመራ ውጤቶች መልካም ናቸው የር. ሊ. ጳ ፍራንችስኮስ የምርመራ ውጤቶች መልካም ናቸው 

የር. ሊ. ጳ ፍራንችስኮስ ሕክምና መልካም ውጤቶችን ማሳየቱ ተነገረ

አስቀድሞ በተያዘላቸው ቀጠሮ መሠረት እሑድ ሰኔ 27/2013 ዓ. ም ከሰዓት በኋላ የሕክምና ዕርዳታን ለማግኘት ወደ ሆስፒታል የሄዱት ር. ሊ. ጳ ፍራንችስኮስ ባሁኑ ወቅት በጥሩ ሁኔታ ላይ መሆናቸውን የቫቲካን ጋዜጣዊ መግለጫ ክፍል ዳይሬክተር አቶ ማቴዎ ብሩኒ አስታውቀዋል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ ዮሐንስ መኰንን - ቫቲካን

ቅዱስነታቸው የቀዶ ጥገና ሕክምና አገልግሎት ከተደረገላቸው በኋላ በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ፣ የሚቀርብላቸውን ቀለል ያሉ ምግቦችን መውሰድ መጀመራቸውን እና የምርመራ ውጤቶችም መልካም መሆናቸውን አቶ ማቴዎ ብሩኒ አስታውቀዋል።

ቅዱስነታቸው ትናንት ሌሊት እና ዛሬ ጥሩ ዕረፍት አድርገው መዋላቸውን እና ጥቂት እንቅስቃሴዎችን ማድረግ መጀመራቸውን የቫቲካን ጋዜጣዊ መግለጫ ክፍሉ ዳይሬክተር አቶ ማቴዎ ብሩኒ አስታውቀዋል።      

06 July 2021, 16:33