ር.ሊ.ጳ.ፍራንቸስኮስ እመንት ሊጀምር የሚገባው ከነጻናት ስሜት ነው
ር.ሊ.ጳ.ፍራንቸስኮስ እመንት ሊጀምር የሚገባው ከነጻናት ስሜት እንጂ ከግዴታ ሊሆን አይገባውም” ማለታቸው ተገለጸ።
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ ዘወትር ረዕቡ እለት በቫቲካን በሚገኘው የጳውሎስ 6ኛ የስብሰባ አዳራሽ ወይም ደግሞ እዳስፈላጊነቱ እና እንደ አየሩ ሁኔታ በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለሚሰበሰቡ ምዕመናን እና የሀገር ጎብኝዎች በተለያዩ አርእስቶች ላይ ተመርኩዘው የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ እንደ ሚያደርጉ ይታወቃል።
በእዚህ መሰረት በዛሬው እለት ማለትም በሰኔ 20/2010 ዓ.ም ያደረጉት የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ ትኩረቱን ያደረገው በኦሪት ዘዳግም በምዕራፍ 4፡32-35 ላይ እንደ ነበረ ለመረዳት የተቻለ ሲሆን የእግዚእብሔር ፍቅር ከሕግ በላይ ሆኖ ሲታይ ትርጉም ይጣል፣ እመንት ሊጀምር የሚገባው ከነጻናት ስሜት እንጂ ከግዴታ ሊሆን አይገባውም” ማለታቸውን ለመረዳት ተችሉዋል።
በእለቱ የተነበበው የምጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ . . .
እግዚአብሔር አምላክ ነው
እግዚአብሔር ሰውን በምድር ላይ ከፈጠረበት ቀን ጀምሮ እናንተ ከመኖራችሁ በፊት ስለ ነበረው የቀድሞ ዘመን ጠይቁ፤ ከአንዱ የሰማይ ጫፍ እስከ ሌላው የሰማይ ጫፍ ድረስ ጠይቅ፤ እንደዚህ ያለ ታላቅ ነገር ከቶ ተደርጎ ወይስ እንደዚህ ዐይነት ነገር ከቶ ተሰምቶ ያውቃልን? ከእሳት ውስጥ እግዚአብሔርን (ኤሎሂም) ድምፅ እንደ እናንተ የሰማና በሕይወት የኖረ ከቶ ሌላ ሕዝብ አለን? አምላካችሁ እግዚአብሔር(ኤሎሂም ያህዌ) በዐይናችሁ እያያችሁ ለእናንተ በግብፅ እንዳደረገው ሁሉ በፈተና፣ በታምራዊ ምልክቶችና በድንቆች፣ በጦርነት፣ በጸናች እጅና በተዘረጋች ክንድ ወይም በታላቅና በአስፈሪ ሥራዎች ከሌላ ሕዝብ መካከል አንድን ሕዝብ የራሱ ለማድረግ የቻለ አምላክ አለን? እግዚአብሔር እርሱ አምላክ (ያህዌ ኤሎሂም) መሆኑን፣ ከእርሱም በቀር ሌላ አምላክ አለመኖሩን ታውቁ ዘንድ እነዚህን ነገሮች እንድታዩ ተደረገ (ኦሪት ዘዳግም 4፡32-35)።
ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በዛሬው ዕለት (ሰኔ 20/2010 ዓ.ም) በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለተሰበሰቡ ምዕመናን ያደርጉትን የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ ሙሉ ይዘት እንደ ሚከተለው ተርጉመነዋል አብራችሁን በመሆን እንድትከታተሉ ከወዲሁ እናጋብዛለን።
የዚህ ዝግጅት አጠናቃሪ-መብራቱ ኃይሌጊዮርጊስ-ቫቲካን
የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንደምን አረፈዳችሁ!