“ክርስቶስ ሕያው ነው” የተሰኘው ሐዋርያዊ ቃለ ምዕዳን በሚስዮናዊ ሕይወት እንድካፈል አድርጎኛል! “ክርስቶስ ሕያው ነው” የተሰኘው ሐዋርያዊ ቃለ ምዕዳን በሚስዮናዊ ሕይወት እንድካፈል አድርጎኛል! 

“ክርስቶስ ሕያው ነው” የተሰኘው ሐዋርያዊ ቃለ ምዕዳን በሚስዮናዊ ሕይወት እንድካፈል አድርጎኛል!

ከመስከረም 23- ጥቅምት 17/2011 ዓ. ም. ድረስ የዛሬ አንድ አመት ገደማ ማለት ነው በቫቲካን 15ኛው የካቶሊክ ቤተ-ክርስቲያን ብጹዕን ጳጳሳት ሲኖዶስ ጠቅላላ መደበኛ ጉባሄ ተካሂዶ ማለፉ የሚታወቅ ሲሆን የዚህ ጉባሄ ማጠቃለያ ሐሳብ “ክርስቶስ ሕያው ነው” በሚል አርእስት የተዘጋጀ ሐዋርያዊ ቃለ ምዕዳን በመጋቢት 16/2011 ዓ. ም. በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ ተፈርሞ ይፋ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን ይህ ቃለ ምዕዳን በመጋቢት 24/2011 ዓ. ም. በይፋ ለንባብ መብቃቱ ይታወሳል።

 አዘጋጅ እና አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ - ቫቲካን

ይህ “ክርስቶስ ሕያው ነው” በሚል አርእስት የተዘጋጀው ሐዋርያዊ ቃለ ምዕዳን ይፋ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ መልኩ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን አባላት የሆኑ ወጣቶች እና እንዲሁም በጎ ፈቃድ ያላቸው ሰዎች ሁሉ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ “ክርስቶስ ሕያው ነው” በሚል አርእስት ይፋ ባደረጉት ሐዋርያዊ ቃለ ምዕዳን ጥሪ በመከተል ለጥሪው ምላሽ በመስጠት በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ በቤተ-ክርስቲያን ተልዕኮ ውስጥ በመሳተፍ ቅዱስ ወንጌልን ለዓለም በማዳረስ ሂደት ውስጥ ተሳታፊ በመሆን ኃላፊነታቸውን በመወጣት ላይ የሚገኙ ብዙ ወጣት ካቶሊክ ምዕመን ሚስዮናዊያን ቁጥር እየተበራከተ መምጣቱም ተገልጹዋል።

ከእነዚህም ውስጥ አንዷ የሆነችው ባርባራ የተባለች ወጣት ይህንን በተመለከተ ስትገልጽ “ወጣት ሚሲዮናዊ ምዕመን በመሆን ክርስቶስን በተለያዩ አጋጣሚዎች መመስከር እንደ ሚቻል፣ በገዳም ሕይወት ውስጥ በመሳተፍ ገድማዊ  ወይም ዳማዊት በመሆን ብቻ ሳይሆን ከእነዚህ መዋቅሮች ውጪ በሆነ መልኩ ወጣቶች በተሰማሩበት የሥራ መስክ ሁሉ በሚስዮናዊ ሕይወት የታጀበ ምዕመን መሆን እንደ ሚችሉ” በመግለጽ በእዚህ ረገድ የበኩሉዋን አስተዋጾ በማበርከት ላይ እንደ ምትገኝ እና “ክርስቶስ ሕያው ነው” የተሰኘው ሐዋርያዊ ቃለ ምዕዳን በሚስዮናዊ ሕይወት እንድካፈል አድርጎኛል ማለቷ ከቫቲካን ዜና ጋር በነበራት ቆይታ መግለጿ ተዘግቡዋል።

በእዚህ “ክርስቶስ ሕያው ነው” በሚለው የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ ሐዋርያዊ ቃለ ምዕዳን ውስጥ ወጣቶች በተሰማሩበት የሥራ መስክ ውስጥ በመሆን በጥምቀት የተሰጣቸውን ሚስዮናዊ የመሆን ኃላፊነት በያሉበት ቦታ ሁነው መወጣት እንደ ሚገባቸው የሚያመለክቱ መልእክቶች በስፋት የተነጸባረቁበት ቃለ ምዕዳን መሆኑ ይታወቃል።

ክርስቶስ ሕያው ነው

 “ክርስቶስ ሕያው ነው! እርሱ ተስፋችን ነው፣ በአስደናቂ መንገድ ወጣቶችን ወደ ዓለማችን ያመጣል።” በቅድሚያ ለእያንዳንዱ ክርስትያን ወጣቶች እነዚህን ቃላት ተጠቅሜ እንዲህ ለማለት እፈልጋለሁ፡ ክርስቶስ ሕያው ነው! እናንተም ሕያው እንድትሆኑ ይፈልጋል”። ይህ ቃል “ክርስቶስ ሕያው ነው” በሚል አርዕስት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ይፋ ያደረጉት ሐዋርያዊ ቃለ ምዕዳን በቅርቡ ቅዱስነታቸው በጣሊያን ግዛት ውስጥ የምትገኘውን የሎሬቶ ከተማ በጎበኙበት ወቅት ለወጣቱ እና ለአጠቃላይ የእግዚኣብሔር ሕዝብ ካስተላለፉት መልእክት የተወሰደ ነው።

ይህ “ክርስቶስ ሕያው ነው” የተሰኘው ሐዋርያዊ ቃለ ምዕዳን 9 ምዕራፎች እና 299 አንቀጾች የተካተቱበት ሐዋርያዊ ቃለ ምዕዳን ሲሆን ይህንን ሐዋርያዊ ቃለ ምዕዳን በተመለከተ ቀድም ሲል ይህ ሐዋርያዊ ቃለ ምዕዳን በሎሬቶ ይፋ በሆነበት ወቅት ቅዱስነታቸው በወቅቱ ባስተላለፉት መልእክት ይህ ሐዋርያዊ ቃለ ምዕዳን እ.አ.አ ባለፈው አመት ጥቅምት ወር ላይ “ከተካሄደው ሲኖዶስ የመነሻ ሐሳብ ተወስዶ እና ዳብሮ የቀረበ” ሐዋርያዊ ቃለ ምዕዳን መሆኑን በወቅቱ ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል።

15 May 2020, 14:03