በቻይና የሚገኙ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ምዕመናን እ.አ.አ 2018 ዓ.ም የገና በዓል ባከበሩበት ወቅት በቻይና የሚገኙ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ምዕመናን እ.አ.አ 2018 ዓ.ም የገና በዓል ባከበሩበት ወቅት  

ቅድስት መንበር እና ቻይና ለሁለት ዓመታት ያህል የሚቆይ ጊዜያዊ ስምምነት መፈራረማቸው ተገለጸ።

ከቅድስት መንበር ፕሬስ ጽሕፈት ቤት በተላለፈው መግለጫ መሰረት “ስምምነቱን በፈጸሙ ወገኖች መካከል ባለው መልካም ግንኙነትና ትብብር መሰረት የተፍረመው ስምምነት አዎንታዊ መሆኑ” ተገልጿል። በቻይና አገር ስለሚገኘው የካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ሹመትን በተመለከተ በቅድስት መንበር እና በቻይና ሕዝባዊ ሪፐብሊክ መካከል ያለው ጊዜያዊ ስምምነት እ.ኤ.አ. በመስከረም 22/2018 ዓ.ም ነበር ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈረመው። እ.ኤ.አ. በመስከረም 22/2018 ዓ.ም ቤጂንግ ውስጥ ተፈርሞ የነበረው ይህ ስምምነት የሁለት አመት የጊዜ ገደብ የተጠናቀቀ ሲሆን ይህ ስምምነት የተፈረመበት ቀን እየተቃረበ ሲመጣ ሁለቱ ወገኖች የስምምነቱን አተገባበር የተለያዩ ገጽታዎች በመገምገም ጊዜውን በይፋ  እ.አ.አ እስከ ጥቅምት 22/2022 ዓ.ም ለሌላ ሁለት ዓመት ለማራዘም ስምምነት ላይ ደርሰዋል። ስምምነቱ ዓላማውን እና ተነሳሽነቱን ለመፈተሽ አጋዥ አጋጣሚ ይመስላል።

አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

በቻይና የጳጳሳትን ሹመት በተመለከተ የተደረገው ይህ ጊዜያዊ ስምምነት ዋና ዓላማ በዚያ ምድር የስብከተ ወንጌል አዋጅ የማስቀጠል እና የማስተዋወቅ ፣ የቤተክርስቲያኗን ሙሉ እና የሚታየውን አንድነት የመመለስ ዓላማ ያነገበ ነው። በእውነቱ በዚህ ሂደት ቅድስት መንበርን ከዚሁ ሀገር መንግስት መሪዎች ጋር በመወያየት የደረሱበት ስምምነት ተቀዳሚ ተነሳሽነቱን የወሰደው መሰረታዊ ከሆነው የቤተክርስቲያን እሴቶች እና ሐዋርያዊ ባሕሪ ያለው ነው። የጳጳሳትን ሹመት አስመልክቶ ጥያቄው በአከባቢያዊም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለቤተክርስቲያኗ ሕይወት አስፈላጊ ጠቀሜታ አለው። በዚህ ረገድ ሁለተኛው የቫቲካን ጉባሄ በቤተክርስቲያኗ ዶግማዊ ህገ-ጋት ላይ “ዘላለማዊ እረኛ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ ራሱ በአብ እንደተላከ ሐዋርያትን በመላክ ቅድስት ቤተክርስቲያኑን አቋቋመ (ዮሐንስ 20: 21)፣ እናም ተተኪዎቻቸው ማለትም ጳጳሳት እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ በቤተክርስቲያኑ ውስጥ እረኞች እንዲሆኑ ፈለገ” በማለት ስለጳጳሳት ሹመት ይናገራል። እናም ኤጲስቆጶሳዊ የሆነው መንፈሳዊ ስልጣን  ራሱ አንድ እና ያልተከፋፈለ እንዲሆን ሐዋርያው ጴጥሮስን ባርኮ ከሌሎቹ ሐዋርያት በላይ አስቀመጠው ፣ በእርሱም ውስጥ ዘላቂ እና ሊታይ የሚችል ምንጭ እና የእምነት እና የኅብረት አንድነት መሠረት አቋቋመ።

የሊቀ ጳጳሳት ልዩ ሚናን ኤጲስቆጶሳዊ ሕብረትን በተመለከተ በተለይም ደግሞ የአቡናትን ሹመት በተመለከተ ይህ መሠረታዊ ትምህርት ድርድሩን ያነቃቃና የስምምነቱ ጽሑፍ ሲዘጋጅ የማጣቀሻ ነጥብ ነበር። ስለሆነም ነገሮች ወደፊት እየገፉ ሲሄዱ፣ የእምነት አንድነትም ሆነ በጳጳሳት መካከል ያለው ህብረት፣ እንዲሁም በቻይና ባለው የካቶሊክ ማህበረሰብ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ መሆን መቻሉን ያረጋግጣል። ከዛሬ ጀምሮ ፣ ከብዙ አሥርተ ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ፣ ​​በቻይና ያሉ ሁሉም ጳጳሳት ከሮማ ጳጳስ ጋር ህብረት ያላቸው ናቸው ፣ እናም በስምምነቱ አፈፃፀም ምስጋና ይግባውና ከዚህ በኋላ ህጋዊ ያልሆኑ የጳጳስ ሹመት በቻይና አይኖርም።

ሆኖም ለቤተክርስቲያኗ አሁንም አሳሳቢ የሆኑ ሁሉም ክፍት ጉዳዮች ወይም ሁኔታዎች በስምምነቱ ውስጥ እንዳልተስተናገዱ ልብ ሊባል ይገባል ፣ ነገር ግን የጳጳሳት ሹመቶች ጉዳይ ብቻ ወሳኝ እና ወሳኝ ለሆነው መደበኛ የክርስትና ሕይወት ዋስትና የሚሰጥ ነው። በወቅቱም ጊዜያዊ ስምምነቱን በተመለከተ የተለያዩ አለመግባባቶች መከሰታቸውን ተጠቁሙዋል። ብዙዎቹ የመነጩት በቻይና ያለውን የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሕይወት አስመልክቶ ያልተለመዱ ዓላማዎች ወይም የማይዛመዱ ክስተቶች በስምምነቱ ውስጥ በመካተታቸው እና እንዲያውም ከእውነተኛው ስምምነት ጋር ከማይገናኙ የፖለቲካ ጉዳዮች ጋር የተቆራኙ በመሆናቸው ነው። ስምምነቱ የጳጳሳትን ሹመት ብቻ የሚመለከት መሆኑን ያስታወሱት የቅድስት መንበር ዋና ጸሐፊ የሆኑት ካርዲናል ፔትሮ ፓሮሊን በቻይና ያለውን የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ሕይወት አስመልክቶ የተለያዩ ችግሮች መኖራቸውን እንደሚያውቁ ገልፀው ፣ ግን ሁሉንም ጉዳዮች በአንድ ላይ መጋፈጥ እንደማይቻል አስረድተዋል።

የቅድስት መንበር እና የቻይና መንግሥት ግንኙነት እየተሻሻለ መምጣቱ ተገለጸ

የቅድስት መንበር የዜና እና የሕትመት ክፍል በቅርቡ ቅድስት መንበር ከቻይና ጋር ያላትን ግንኙነት በተመለከተ ባወጣው መገለጫ እንደ ገለጸው ከቻይና መንገሥት ጋር ቅድስት መንበር በተከታታይ እያደርገችው የሚገኘው የዲፕሎማሲ ግንኙነት ወደ አንድ ወሳኝ አዎንታዊ እርማጃ እየተለወጠ መሄዱን የሚያሳዩ በርካት ምልክቶች እንደ ሚታዩ ማስታወቁ ይታወሳል።

በቻይና እና በቅድስት መንበረ መካከል ያለው ግንኙነት ይበልጡኑ ለማጠናከር በማሰብ በቅርቡ በሮም ከተማ በሁለቱ ማለትም የቅድስት መንበር እና የቻይና የመንግሥት ተወካዮች ተገናኝተው መምከራቸውን ያወሳው የቅድስት መንበር የሕትመት እና የዜና ክፍል መግለጫ የካቶሊክ ቤተክርስቲያንን በተመለከተ ከቻይና  መንግሥት ጋር በጥል እና በክርክር መንፈስ ሳይሆን ገንቢ በሆነ ሁኔታ ድርድሮች እየተደረጉ እና መግባባቶች እየተፈጠሩ መሆናቸውን መገለጫው ጨምሮ የገለጸ ሲሆን በተለይም ደግሞ ቅድስት መንበር በቻይና የካቶሊክ ጳጳስ ለመሾም ያላት ፍላጎትን በተመለከተ የቻይና መንግስት አቋም አሁኑም ጠንካራ በመሆኑ የተነሳ በቻይና የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጳጳስ ለመሾም እየተደርገ ያለው ውይይት አሁንም ያልተፈታ በመሆኑ የተነሳ በጥል መንፈስ ሳይሆን በመግባባት መንፈስ አሁኑም ድርድሩ እንደ ቀጠለ ለመረዳት ተችሉዋል።

በአሁኑ ወቅት በቻይና መንግሥት እና በቫቲካን መካከል ያለው ግንኙነት ጥሩ የሚባል ደረጃ ላይ ቢሆንም በሁለቱ ሀገራት መካከል የሚደረገው ውይይት ኦፊሴላዊ በሆነ መንገድ ብቻ ሳይሆን በሐዋርያዊ ተግባርም ሳይቀር መደገፍ ያለበት በመሆኑ የተነሳ አንድ ጊዜ ምህታታዊ በሆነ መልኩ ወደ አንድ አምርቂ ውጤት የሚቀየር ሳይሆን  ቀስ በቀስ በሂደት የሚመጣ እንደ ሆነም ከቅድስት መንበር የዜና እና የሕትመት ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።

ካርዲናል ፔትሮ ፓሮሊን “ቫቲካን ከቻይና መንግሥት ጋር የምታደርገውን ውይይት አጠናክራ ትቀጥላለች”

ከ19ኛው እስከ 21ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ “ቫቲካን ከሌሎች አገራት ጋር ያደረገቻቸው ስምምነቶች” በሚል መሪ ቃል ከየካቲ 21/2011 ዓ.ም በግሪጎሪያን ጳጳሳዊ ዩኒቬርሲቲ የተካሄደው ዓለም አቀፍ ጉባሄ ላይ ተገኝተው የነበሩት በቫቲካን የቅድስት መንበር ዋና ጸሐፊ የሆኑት ካርዲናል ፔትሮ ፓሮሊን በወቅቱ ባደረጉት ንግግር እንደ ገለጹት በተለይም ደግሞ ከቻይና ሪፖብሊክ ጋር የካቶሊክ ቤተክርስቲያን የምታደርገው ቀጣይነት ያለው ውይይት ለረጅም ጊዜ ከፍተኛ ሥራ ሲሰራበት የቆየ ጉዳይ እንደ ሆነ ገልጸው ለቤተ ክርስቲያኗ እና ለአገሪቱ ለቻይና ሪፖብሊክ  መልካም ፍሬ ማፍራት እንደሚችል ተስፋ እናደርጋለን ማለታቸው ይታወሳል። በመቀጠልም ከቫቲካን ጋር እስካሁን ድረስ ስምምነት የሌላቸው የአፍሪካ አገራት ጋር ስምምነት ይፈረም ዘንድ ቫቲካን ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ እንደ ሆነች ጨምረው ገልጸዋል።

ከቻይና ጋር እ.አ.አ. በመስከረም 22/2018 ዓ.ም በቤጅንግ የተፈረመውን ስምምነት ተግባራዊ በሆነ መልኩ ለመጀመር “በአሁኑ ጊዜ በቻይና ውስጥ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጳጳሳት ሹመትን ለመፈፀም የሚያስችል ጊዜያዊ ስምምነት ማድረጉ አስፈላጊ ነው፣ በዚህም የስምምነቱን ተግባራዊነት ማረጋገጥ ይቻላል” በማለት ከጉባሄው በኋላ በተለይ ለቫቲካን ዜና የተናገሩት ካርዲናል ፓሮሊን “ይህ ረጅም ጊዜ የፈጀ ሥራ የተካሄደበት  ምክኛት በመጨረሻም ለእኛ ቤተክርስቲያን እና ለአገሪቱ መልካም ፍሬዎች የሚያስገኙ ውጤቶችን ማምጣት እንችላለን ብለን ተስፋ የምናደርግበት ስምምነት ስለሆነ ነው” ብለዋል።

መግባባት ላይ ያልተደርሰባቸው ሁለት ጉዳዮች

“ለሐይማኖት ዝግ ከሆነ አገር ወደ የሐይማኖት ነጻነት”  የሚሉት ሁለት ዋና ዋና ጉዳዮች ከቻይና መንግሥት ጋር በተደረገው ስምምነት ላይ "እነዚህ ሁለት ጉዳዮች በሁለቱም ወገኖች የጋራ አቋም ላይ ተደርሶ ዕውቅና ያልተሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸውን” የገለጹት ካርዲና ፔትሮ ፓሮሊን እነዚህ አስፈላጊና ዋና ዋና የሆኑ ጉዳዮች በቀጣይነት ውይይት የሚደርግባቸው እንደ ሆነ ጨምረው ገልጸዋል።

ለሐይማኖት ነፃነት እና ለጋራ ጥቅም የተደርጉ ስምምነቶች

“የሐይማኖት ነጻነትን በመለከተ ቤተክርስቲያን ተልዕኮዋን ያለምንም ጣልቃ ገብነት በቻይና ማከናወን ትችል ዘንድ በተዳጋጋሚ ጥያቄ መቅረቡን”  የገለጹት ካርዲናል ፔትሮ ፓሮሊን ይህም ጥያቄ የካቶሊክ እምነትን ብቻ የተመለከተ ጉዳይ ሳይሆን የማነኛውም ዓይነት ሐይማኖት ተከታይ በቻይና እምነቱን በነጻነት ያካሂድ ዘንድ የሚጠይቅ እንደ ሆነ ገልጸው ይህም ለአገሪቷ እና ለሕዝቦቿ ጭምር በሁለተኛው የቫቲካን ጉባሄ ሰንድ ላይ በላቲን ቋንቋ “Gaudium et spes” ላይ እንደ ተጠቀሰው “በተቀናጀ መልኩ ሁለንተናዊ ማለትም መንፈሳዊ እና ቁሳዊ ልማትን ለማጎልበት እና ሰላምን ለማጠናከር የሚረዳ” መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል።

በቁጥር አነስተኛ ካቶሊኮች የሚኖሩባቸው አገራት

በቁጥር አነስተኛ የሆኑ የካቶሊክ ምዕመናን ከሚኖሩባቸው አገራት ጋር ስምምነት ማደርግን በተመለከተ የተናገሩት ካርዲናል ፔትሮ ፓሮሊን እ.አ.አ 1964 ዓ.ም ከቱኒዚያ ጋር፣ እ.አ.አ. 1983 ዓ.ም ከሞሮኮ ጋር፣ እ.አ.አ. 1993 ከእስራኤል ጋር፣ በመጨረሻም እ.አ.አ 2015 ዓ.ም ከፍልስጤም ጋር የተፈረሙ ስምምነቶች እንደ ሚገኙ የገለጹት ካርዲናል ፔትሮ ፓሮሊን ባለፉት አመታት ውስጥ ቫቲካን ክርስቲያን ካልሆኑ አገራት ጋር ጭምር ስምምነት ለመፈራረም ሙከራ ማድረጓን ጨምረው ገልጸዋል። 

ቫቲካን ከቻይና መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር ውይይት የምታደርገው ለምንድነው? ቅድስት መንበር ከቻይና መንግሥት ጋር የምታደርገውን ውይይት የጋራ መተማመን ላይ ለመድረስ የሚያስችሉ አስፈላጊ እርምጃዎች ናቸው። በቻይና የሚኖሩ የካቶሊክ እመነት ተከታይ የሆኑ ምዕመናን ምንም እንኳን በሐይማኖታቸው የተነሳ ከፍተኛ የሆነ ስቃይ ቢደርስባቸውም ለእምነታቸው ታማኝ ሆነው ቆይተዋል። ታዲያ እንደነዚህ ዓይነት ውይይቶች ምን ሊያስገኙ ይችላሉ?

ውይይቶች ለቤተክርስቲያን አስፈላጊ ናቸው!

ውይይቶች ለቤተክርስቲያን ሕይወት መሠረታዊ የሆኑ እና አስፈላጊ ነገሮች ናቸው። ውይይት በቤተክርስቲያኗ ውስጥም ሆነ በአለም ውስጥ ካለው ግንኙነት አኳያ የቤተክርስቲያኗን የአኗኗር ዘዴ የሚደግፍ አስፈላጊ ነገር ነው። መወያየት ማለት ከሕብረተሰብ፣ ከሃይማኖቶች እና ከባህሎች ጋር ግንኙነት መፍጠር ማለት ነው። የሁለተኛው የቫቲካን ጉባሄ ሰነድ እንደ ሚያመለክተው “ውይይት ሐዋርያዊ የሆነ ተግባር መሆኑን” የገለጸ ሲሆን ይህ ውይይት በብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ብቻ የሚካሄድ ሳይሆን፣ ነገር ግን ክርስቲያን ካልሆኑ የማኅበርሰብ ክፍሎች፣ ከሲቪል ባለስልጣኖች እና ከሁሉም በጎ ፈቃድ ካላቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች ጋር የሚደረግ እንደ ሆነ ይገልጻል። ከሁለተኛው የቫቲካን ጉባሄ ሰነዶች መካከል “በዚህ ዘመን የምትገኝ ቤተ ክርስቲያን” በላቲን ቋንቋ (Gaudium et Spes no.21) በተሰኘው ሰነድ ውስጥ ይህንን ጉዳይ በተመለከተ እንዳሰፈረው “ለሁሉም ሰዎች፣ አማኞች እና እምነት የሌላቸው ሰዎች ጭምር አብሮ የሚኖሩባትን ዓለም ለመገንባት ለሚደረገው ጥረት የራሳቸውን አስተዋጾ ማድረግ ይኖርባቸዋል፣ ይህ ያለ እውነተኛ እና በጥበብ መንፈስ ከሚደረግ ውይይት ውጪ እውን ሊሆን አይችልም” (21) ይላል።

“ቤተክርስቲያን ራሷ ከምትገኝበት ከአለም ጋር መወያየት ይኖርባታል

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ጳውሎስ 6ኛ በላቲን ቋንቋ “Ecclesiam Suam” በአማሪኛው በግርድፉ ሲተረጎም (የራሱ (የክርቶስ) ቤተክርስቲያን) በሚል አርእስት በጻፉት ሐዋርያዊ መልእክት ላይ ይህንን በተመለከተ ተመሳሳይ በሆነ መልኩ “ቤተክርስቲያን ራሷ ከምትገኝበት ከአለም ጋር መወያየት ይኖርባታል። ቤተክርስቲያን ስትናገር ራሷ መልእክት ትሆናለች” (ቁ.67) በማለት ይገልጻሉ። የካቶሊክ ቤተክርስቲያን “መልካም ፈቃድ ካላቸው፣ በራሷ ውስጥ ካሉ ሰዎች ጋር ይሁን ከራሷ ውጪ ካሉ ሰዎች ጋር የሚደረጉትን ውይይቶች ለመደገፍ ዝግጁ ናት” (97)።

በሰዎች፣ በተቋማት እና በማህበረሰቦች መካከል የሚደረጉ ውይይቶች የጓደኝነት ስሜት ሊፈጥሩ የሚችሉ የእውቀት ሽግግር እንዲኖር ያደርጋሉ። በማነኛውም ሁኔታ ገንቢ የሆነ ውይይት ለማድረግ በቅድሚያ መተማመን ያስፈልጋል። የጋራ መተማመን የብዙ ትናንሽ የሚባሉ እርማጃዎች፣ እንቅስቃሴዎች እና ግንኙነቶች ፍሬ ሲሆን ይህም በተደጋገሚ በረጋ መንፈስ እና በከፍተኛ ጥበብ የሚፈጸም ተግባር ሊሆን ይገባል። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ በግንቦት 8/2009 ዓ.ም እንደ ተናገሩት “ሁልጊዜም ቢሆን ያልተዘጉ በሮች አሉ" በማለት ሁሌም ለውይይት በራችንን መክፈት እንደ ሚገባን ያመለክታሉ።

ቤተክርስቲያን ከቻይና መንግሥት ጋር የምታደርገው ውይይት ግልጽ የሆነ አቅጣጫ ያስፈልገዋል

በቅርብ ጊዜያት የነበሩት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ለምሳሌም ብጹዕ ጳውሎስ 6ኛ ከቻይና ጋር ጥንቃቄ የተሞላ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዲጀመር በማድረግ በቀጣይነት ቅዱስ ዮሐንስ ጳውሎስ እና የቀድሞ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በነዴክቶስ 16ኛ ከቻይና መንግሥት ጋር የሚደረገውን ውይይት ውጤታማ እንዲሆን ግልጽ አቅጣጫ በመስቀመጣቸው የተነሳ  ምስጋና ይድረሳቸውና በአሁኑ ወቅት በቅድስት መንበር እና በቻይና መንግሥት መካከል በተወሰነ መልኩም ቢሆን ውይይት ለማድረግ የተቻለ ሲሆን እያንዳንዱ ውይይት የራሱ የሆነ አዲስ መንገድ የከፈተ እና በሚገነባው የጋራ ግንኙነት ላይ የራሱን አዲስ የመሰረት ድንጋይ ያስቀመጠ በተስፋ የተሞላ የማነቃቂያ ሐሳቦችን ያፈለቀ እና እንቅስቃሴዎች እንዲጀመሩ ያስቻለ አጋጣሚ ነው። በጣም በቅርብ ጊዜ የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስን ግላዊ ሕይወት፣ አስተምህሮ እና አቀራረብ በመመልከት ቻይናን ጨምሮ በብዙ ሕዝቦች እና ሀገራት ውስጥ የሚኖሩ ሁሉ የውይይት መድረኮች እንዲከፈቱ በማበረታታት ላይ ናቸው።

ቤተክርስቲያን የምታደርጋቸው ውይይቶች በእውነት ላይ የተመሰረቱ ናቸው  

የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ውይይትን በራሱ እንደ አንድ መቋጫ ወይም መደምደሚያ ግብ አድርጋ አትመለከትም። ያላትን ሁሉ አቅም ተጠቅማ የፖለቲካ እና የዲፕሎማሲ ጥቅሞችን ለማግኘት “አስፈላጊ የሆኑትን መሰረታዊ መርሆች አሳልፋ ለመስጠት ተዘጋጅታለች ማለትም አይደለም። ይህንን ጉዳይ ከቻይና ጋር በተያያዘ መልኩ ስንመለከተው በቻይና በሚገኙ የካቶሊክ ማኅበርሰቦች ላይ የደረሰውን  መከራ መርሳት ማለት አይደለም። ቤተ ክርስቲያን የምታደርጋቸው ውይይቶች ሁልጊዜም ቢሆን በእውነት እና በፍትህ ላይ የተመሰረቱ፣ ከሰው ልጅ ጋር ሊነጣጠል በፍጹም የማይችለውን መልካም ጎን እና መሠረታዊ መብቶችን በማስከበር ላይ የተመሰረቱ መሆን አለባቸው። አንድ ግልጽ ሊሆን የሚገባው አስፈላጊ ነገር ቤተክርስቲያን በቻይና የምታደገው ተልዕኮ የመንግሥት መዋቅሮችን ወይም አስተዳደሮችን ለመቀየር ወይም የፖለቲካ ኃይል ለማዋቀር ወይም ባለሥልጣኖችን ለመቃወም ያለመ እንዳልሆን ልብ ሊባል ይገባዋል። ቤተክርስቲያን ተልዕኮዋን  በፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች አከባቢ የምታደግ ከሆነ የራሷን ትክክለኛ ማንነት በመካድ ከብዙ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ ልክ እንደ አንዱ ተፎካካሪ ፓርቲ በመሆን፣ መለኮታዊ የሆነውን ጥሪ በመርሳት ወይም በመካድ፣ በእንደነዚህ ዓይነት እንቅስቃሴዎች ውስጥ በመግባት ለጊዜያዊ ጥቅሞች ማስፈጸሚያንት ያለሙ ተግባራት ውስጥ በፍጹም አትሳተፍም።

ቤተክርስቲያን ትክክለኛ እና ሐቀኛ የሆኑ ውይይቶችን ማድረግ ትፈልጋለች

ትክክለኛ እና ሐቀኛ የሆኑ ውይይቶች ቤተክርስቲያን በማኅበርሰቡ ውስጥ ሆና መሥራት እንድትችል የሚያደርጋት ሲሆን ይህም ለካቶሊክ ቤተክርስቲያን ምዕመናን ሕጋዊ የሆነ ጥበቃዎችን በማድረግ የጋራ ጥቅሞች ዙሪያ እንድትሠራ ያስችላታል። በዚህ አግባብ ቤተክርስቲያን የትችት/ሂስ ቃላቶችን በምትናገርበት ወቅት ዓላማዋ ውዝግብ ለመፍጠር ሳይሆን ትክክለኛ እና ገንቢ መንፈስ ያለው ኅብረተሰብ ለመፍጠር በማሰብ የምታደገው ነው። ትችቶች/ሂስ ተጨባጭ የሆኑ የሐዋሪያዊ ሥራዎች የፍቅር መገለጫ ተመክሮዎች ተደርገው ሊቆጠሩ ይችላሉ፣ ምክንያቱም ደካማ የሆኑ ሰዎችን ስቃይ፣ ድምጻቸውን ለማሰማት የተሳናቸው ሰዎች ድምጻቸው እንዲሰማ ጥንካሬን ስለሚፈጥር ነው።

ቅድስት መንበር ከቻይና ጋር በእውነተኛ መንፈስ የሚደረጉ ውይይቶችን አጠናክራ ትቀጥላለች

ከቻይና ጋር በተያያዘ መልኩ የቅድስት መንበር ያላት አቋም እና እምነት በአክብሮት እና በእውነተኛ መንፈስ የሚደረጉ ውይይቶች ምንም ያህል አስቸጋር እና አደገኛ ቢሆኑም እንኳን በእዚህ አኳኅን የሚደረጉ ውይይቶች እንዲካሄዱ ምቹ የሆኑ ሁኔታዎች በማሰናዳት እንዲካሄዱ የምትጥር ሲሆን ቀጣይነት ባለው መልኩ ውይይቶችን በማድረግ ሐሳቦችን በመቀያየር እና በመግባባት ግንዛቤን በመፍጠር በመኃል ያሉትን አለመግባባቶችን በመፍታት ገንቢ የሆነ ግንኙነት እንደ ሚፈጠር ታምናለች።

ቫቲካን በተለሳለሰ መልኩ የምታከናውነውን ተግባር ቻይና በጥንቃቄ ትመለከተዋለች

ቅድስት መንበር “በተለሳለሰ ኃይል” በዓለም ደረጃ እያከናወነች የምትገኘውን እንቅስቃሴ ቻይና ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ እየተከታተለች መሆኑን የሚያሳዩ የተለያዩ ምልክቶች አሉ። የቻይና ታሪክ በተመሳሳይ መልኩ እየቀጠለ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን  በቤተክርስቲያን ውስጥ በከፍተኛ የኃላፊነት ቦታ ላይ የሚሠሩ ሰዎች በጥበብ የተሞላ ውሳኔዎችን ማድረግ ይኖርባቸዋል። የቅድስት መንበር ከቻይና መንግሥት ጋር ለሩብ ምዕተ አመታት ያህል ውይይት ስታደግ የቆየችሁ በዚሁ ምክንያት ነው፣ በዘመናት ውስጥ ያሉትን ምልክቶች ለማንበብ ለሚፈልጉ እና በታሪክ ውስጥ የእግዚአብሔርን መገኘት ለመገንዘብ ለሚፈልጉ ሰዎች ሁሉ የቤተክርስቲያኗ ሐዋርያዊ ዓላማ ይህ መሆኑን ያሳያል።

የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ከቻይና መንግሥት ጋር በቻይና የሚገኙትን የካቶሊክ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮችን በተመለከተ በተደጋጋሚ ውይይት እያደረገች እንደ ምትገኝ የሚታወቅ ሲሆን በቻይና የሚገኙትን የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን ጉዳይ በተመለከተ ከዚህ ቀደም በርካታ ውይይቶች ከቻይና መንግሥት ጋር መደረጋቸው ይታወሳል።

ይህንን በተመለከተ ደግሞ በተለያዩ ጊዜያት የነበሩ የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ርዕሳነ ሊቃነ ጳጳሳት አቋም የኮሚኒስት ርዕዮተ ዓለም አራማጅ የሆኑ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የሚንጸባረቁ እና በቤተክርስቲያኗ ተቀባይነት የሌላቸው ጽንሰ-ሐሳቦችን በተመለከተ በሁለቱ አገራት (በቫቲኻን እና በቻይና) መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ለማሻሻል የሚደረጉ ጥረቶች ተደጋጋሚ ውይይቶችን በማደርግ መልካም የሆነ ውጤት ማምጣት እንደ ሚቻል የሚገልጽ አቋም እያራማዱ እንደ ሆነም ይታወቃል።

23 October 2020, 20:15