የሐይማኖት አባቶች የጸሎት ቀን በሮም ከተማ የሐይማኖት አባቶች የጸሎት ቀን በሮም ከተማ 

ር.ሊ.ጳ ፍራንቸስኮስ ሰላማዊ የሆነ ዓለም በመገንባት በጋራ ወደ ደህንነት መነገድ መራመድ ይቻላል አሉ

በሮም ከተማ በሚገኘው እና የካፕዲዮሎ አደባባይ በመባል በሚታወቀው ስፍራ ላይ ትላንት ጥቅምት 10/2013 ዓ.ም ላይ ከዓለም ዙሪያ የተውጣጡ የሃይማኖት መሪዎች በተገኙበት በመላው ዓለም ሰላም እና የወንድማማችነት መንፈስ ይጠናከር ዘንድ ጸሎት የተደረገ ሲሆን በዚህ ዝግጅት ላይ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ ባደረጉት ንግግር እንደ ገለጹት “ጦርነትን ማስቆም ሁሉም የፖለቲካ መሪዎች በእግዚአብሔር ፊት የተሰጣቸው አስፈላጊ ግዴታ ነው” ሲሉ መናገራቸው ተገልጿል።

የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ ቫቲካን

ቅዱስ ሄጂዲዮ የተባለ አንድ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ግብረ ሰናይ ድርጅት ባዘጋጀው በዚህ ዓለም አቀፍ የሰላም ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ የተሰበሰቡት የሃይማኖት መሪዎችን ድምጾች እና ተስፋዎችን በመላው ዓለም ያስተጋ ስብሰባ ነበር። በስብሰባው ላይ የጣሊያን ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሰርጂዮ ማትሬላን ጨምሮ በርካታ ባለሥልጣናት ፊት በበርካታ ቋንቋዎች ሃይማኖታዊ መዝሙሮች የተሰሙ ሲሆን በተለያዩ ቋንቋዎች እና እምነቶች የሰላም ተምሳሌት ሆነው በአንድነት ያሳለፉት ምሽት ነበር።

በወቅቱ ከማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ 15 ላይ ተወስዶ በተነበበው እና የኢየሱስን ስቅለት በሚተርከው የመጽሀፍ ቅዱስ ክፍል ላይ ተንተርሰው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ  ያደረጉትን የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ ሙሉ ይዘቱን እንደሚከተለው እናቀርበዋለን፣ ተከታተሉን።

አብሮ መጸለይ ስጦታ ነው። ሁላችሁንም በተለይም ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ወንድሜ በርተሎሜዎስ እና በጀርመን የወንጌላውያን ቤተክርስቲያን ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ውድ አቡነ ሄንሪክ፣ ሁላችሁንም በፍቅር አመሰግናለሁ እንዲሁም ሰላምታ አቀርብላችኋለሁ። እንደ አለመታደል ሆኖ የካንተርበሪ እጅግ የተከበሩ ሊቀ ጳጳስ ጄስቲን በወረርሽኙ ምክንያት እዚህ መምጣት አልቻሉም።

አሁን ካዳመጥነው እና የጌታን ሕማማት ከሚተርከው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የተወሰደው ምንባብ ውስጥ ኢየሱስ ከመሞቱ ጥቂት ቀደም ብሎ የሚገኝ ታሪክ ሲሆን በመስቀል ላይ ስለሚገጥመው ስቃይ እና በእሱ ላይ ስለሚደርሰው ፈተና ይናገራል። ከፍተኛ የሆነ ሕማም ውስጥ እና የፍቅር ምስጢር ውስጥ በነበረበት ወቅት ብዙ ሰዎች ያለምንም ርህራሄ “ራስህን አድን! (ማርቆስ 15፡30) እያሉ ያፌዙበት ነበር። እሱ በጣም ከባድ ፈተና ነው ፣ ይህም ሁሉንም ሰው ፣ እኛ ክርስቲያኖችም ጭምር የሚያዳክም ነው -የራስን ወይም የቡድንን ደህንነት ለመጠበቅ ብቻ ማሰብ ፣ የራሳቸውን ችግሮች እና ፍላጎቶች ብቻ በአእምሯችን ማሰብ፣ የሌሎች ሰዎች ችግር ከምንም አለምቁጠር የመሳሰሉ ፈተናዎች ያጋጥሙናል። ይህም እጅግ በጣም የሰው ልጆችን ተፈጥሮአዊ ባሕሪ የሚንጸባርቅ ነገር ቢሆንም፣ ነገር ግን መጥፎ የሆነ ነገር ነው፣ እናም ለተሰቀለው አምላክ የመጨረሻ ፈተና ነው።

ራስህን አድን። በእዚያ በኩል የሚያልፉ ሰዎች ሁሉ ይህንን ይሉት ነበር። እነዚህ ሰዎች ኢየሱስ ሲያስተምር እና ድንቅ ነገሮችን ሲያከናውን የሰሙ እና ያዩ የማሕበርሰብ ክፍሎች ነበሩ። አሁን ደግሞ “እስቲ አሁን ከመስቀል ውረድና ራስህን አድን” እያሉ ያፌዙበታል። ከመስቀል ሲወርድ ለማየት መፈለጋቸው ተአምራት ለማየት ካላቸው ፍላጎት የተነሳ ነው እንጂ ለእርሱ ርህራሄ ስለተሰማቸው ግን አልንበረም። ምናልባት እኛ ደግሞ አንዳንድ ጊዜ ርህሩህ የሆነ ሳይሆን ድንቅ ነገሮችን የሚያደርግ አስደናቂ የሆነ አምላክ ለማየት እንመርጣለን፣ በዓለም ፊት እጅግ በጣም ኃያል አምላክ የሆነውን እንመርጣለን፣ እሱ በኃይል የሚጫን እና እኛን የሚጎዱንን በሙሉ በኃይል የሚያሸንፈውን እግዚአብሔር እንመርጣለን። ነገር ግን የአዚህ ዓይነቱ እግዚአብሔር የእኛ አምላክ አይደለም። ብዙን ጊዜ እኛ ወደ እግዚአብሔር ልኬት እራሳችንን ከመውሰድ ይልቅ አምላክ በእኛ ልክ እንዲሆን እንፈልጋለን፣ እንደ እርሱ ከመሆን ይልቅ እንደ እኛ ያለ አምላክ እንፈልጋለን! ነገር ግን በዚህ መንገድ ከእግዚአብሄር አምልኮ ይልቅ የራስን አምልኮ እንመርጣለን። በእዚህ ሁኔታ የምንሄድ ከሆነ እግዚአብሔርን ከማምለክ ይልቅ እራሳችንን ወደ ማምልከ እንሄዳለን። በእዚህ መልክ እያደገ የሚሄደው የግል አምልኮ ሌሎችን በግድዬለሽነት እንድንመለከት ያደርገናል። በእርግጥ እነዚያ አላፊ አግዳሚዎች ፍላጎታቸውን ለማርካት ብቻ ይሹ ነበር። ኢየሱስ በመስቀል ላይ መሆኑ የትንሽነት ምልክት መስሎ ስለተሰማቸው እንዲያው ለእርሱ ብዙ ግድ አልነበራቸውም፤ ከእንግዲህ ለእርሱ ፍላጎት አልነበራቸውም ነበር። በዓይናቸው ስር ነበር፣ ነገር ግን ከልባቸው የራቀ ነበር። ግድየለሽነት ከእውነተኛው የእግዚአብሔር ፊት እንዲርቁ አደረጋቸው።

ራስህን አድን። በሁለተኛ ደረጃ የካህናት አለቆች እና ጸሐፍት ወደ ፊት ይመጣሉ። ኢየሱስ በእነርሱ ላይ አደጋ የጋረጠ ስለመሰላቸው እንዲፈረድበት ያደረጉት እነርሱ ነበሩ።  እኛ ግን እራሳችንን ለማዳን ሌሎች በመስቀል ላይ እዲከነቸሩ ማድረግ የተካንን ነን። በሌላ በኩል ኢየሱስ በሌሎች ላይ ክፉ እንዳናደርግ እኛን ለማስተማር ራሱን በምስማር እዲቸነክሩት ፈቀደ። እነዚያ የሃይማኖት መሪዎች በሌሎች ምክንያት ነበር ኢየሱስን “ሌሎችን አዳነ ራሱን ግን ማዳን አልቻለም!” በማለት ይከሱት የነበረው። እነሱ ኢየሱስን ያውቁታል ፣ እርሱ ያደረጋቸውን ፈውሶች እና ነፃ ያወጣቸውን ሰዎች ያስታውሳሉ፣ ነገር ግን ተንኮል አዘል ትስስር ይፈጥራሉ- ማዳን ፣ ሌሎችን መርዳት ምንም መልካም ነገር አያመጣም ብለው ያስባሉ። ለሌሎች ብዙ ያደረገው እርሱ ራሱን እያጣ ነው! ክሱ ሁለት ጊዜ “አዳነ” የሚለውን ሐያማኖታዊ ግስ የተጠቀመ ሲሆን መሳለቂያ እና ሐይማኖታዊ ቃላትን ይጠቀማል። ነገር ግን ራስን የማዳን “ወንጌል” የመዳን ወንጌል አይደለም። እሱ በሌሎች ላይ መስቀሎችን የሚያኖር በጣም ውሸታም የሆነ ወንጌል ነው። እውነተኛው ወንጌል በሌላ በኩል የሌሎችን መስቀሎች ወስዶ ይሸከማል።

ራስህን አድን። በመጨረሻም ከኢየሱስ ጋር የተሰቀሉት እንኳን ሳይቀሩ በእርሱ ላይ የጥርጣሬ ስሜት ያንጸባርቁ ነበር። በደካሞች እና በጣም በተገለሉ ሰዎች ላይ ጥፋተኛውን እስከማወርድ ድረስ በቀላሉ መተቸት ፣ መቃወም ፣ በራስ ላይ ሳይሆን በሌሎች ላይ ያለውን ክፋት ማየት እንዴት ቀላል ነው! ነገር  ግን እነዚያ ከእርሱ ጋር የተሰቀሉትን ሰዎች ኢየሱስ ለምን አላዳነንም? ለምን ከመስቀል ላይ አላወረደንም በማለት እነርሱም ይሳልቁበት ነበር። እነሱም “እራስህን እና እኛንም አድን!” ይሉት ነበር (ሉቃስ 23፡39)። ችግሮቻቸውን ለመፍታት ብቻ ኢየሱስን ይፈልጉታል። ነገር ግን እግዚአብሔር የመጣው ብዙ ጊዜ ከሚከሰቱ ችግሮች እኛን ለማዳን አይደለም፣ ነገር ግን ከእውነተኛው ችግር እኛን ለማዳን ነው ፣ ይህም የፍቅር እጦት ነው። ለግል ፣ ለማህበራዊ ፣ ለአለም አቀፍ እና ለአካባቢያዊ ህመሞች መንስኤ የሆነው የፍቅር እጦት ነው። ስለ ራስ ብቻ ማሰብ የክፋት ሁሉ አባት ነው። ነገር ግን ከወንጀለኞቹ አንዱ ኢየሱስን ተመልክቶ መለስተኛ ፍቅር በእርሱ ውስጥ አየ። እናም ይህ ሰው አንድ ነገር ብቻ በማድረግ መንግሰተ ሰማያትን ያገኛል - ትኩረቱን ከራሱ ወደ ኢየሱስ በማዞር ፣ ከራሱ ወደ እርሱ አጠገብ ወደነበረው ወደ ኢየሱስ በማዞር መንግሥተ ሰማይ ይወርሳል (ሉቃስ 23፡ 42)።

ውድ ወንድሞች እና እህቶች ፣ እኛን ለማዳን በመጣው በእግዚአብሔር እና እራሱን ለማዳን በሚፈልግ ሰው መካከል ታላቅ ውዝግብ በቀራኒዮ ተካሂዷል ፣ በእግዚአብሔር እና በራስ አምልኮ መካከል ባለው እምነት መካከል፤ ከሳሽ በሆነው በሰው እና ይቅር ባይ በሆነው በእግዚአብሔር መካከል። እናም የእግዚአብሔር ድል መጣ፣ ምህረቱ በዓለም ላይ ወረደ። ይቅር ባይነት ከመስቀሉ ፈሰሰ ፣ ወንድማማችነት እንደገና ተወለደ-“መስቀሉ ወንድማማቾች ያደርገናል”።  በመስቀል ላይ የተከፈቱት የኢየሱስ ክንዶች የመዞሪያ ነጥቡን ያመለክታሉ፣ ምክንያቱም እግዚአብሔር ጣትን ወደ አንድ ሰው አይጠቁም፣ ነገር ግን ሁሉንም ያቅፋል። ምክንያቱም ጥላቻን የሚያጠፋው ፍቅር ብቻ ስለሆነ እስከ መጨረሻው ኢ-ፍትሃዊነትን የሚያሸንፈው ፍቅር ብቻ ነው። ለሌላ ቦታ የሚሰጥው ፍቅር ብቻ ነው። በመካከላችን ወደ ሙሉ ህብረት የሚወስደው መንገድ ፍቅር ብቻ ነው።

እስቲ የተሰቀለውን እግዚአብሔርን እንመልከት እና የተሰቀለውን እግዚአብሔር የበለጠ አንድነት ፣ የበለጠ ወንድማዊ እንዲሆን ጸጋውን እንለምነው። እናም የዓለምን አመክንዮ ለመከተል ስንፈተን የኢየሱስን ቃላት እናስታውሳለን-«ነፍሱን ለማዳን የሚፈልግ ሁሉ ያጠፋታል ፣ ስለ እኔና ስለ ወንጌል ነፍሱን የሚያጠፋ ሁሉ ግን ያድናታል ”(ማርቆስ 8፡ 35)። በሰው ፊት ኪሳራ የሆነው ነገር ለእኛ መዳን ነው። እኛ ራሱን ባዶ በማድረግ ካዳነን ከጌታ እንማራለን (ፊል 2፡7) እርሱ ደግሞ “ሌሎች እንድንሆን” ፣ ወደ ሌሎች እንድንሄድ ይጋብዘናል ፡፡ ከጌታ ከኢየሱስ ጋር በተያያዝን መጠን የበለጠ ክፍት እና “ሁለንተናዊ” እንሆናለን ፣ ምክንያቱም ለሌሎች ኃላፊነት እንደሚሰማን ያደርገናል። ሌላው ደግሞ ራስን ለማዳን መንገድ ይሆናል - እያንዳንዱ ሌላ ፣ እያንዳንዱ ሰብዓዊ ፍጡር ፣ ታሪኩ እና እምነቱ ምንም ይሁን ምን ልናድነው ይገባል። ከድሆች ጀምሮ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በጣም ተመሳሳይ ናቸው። የታላቁ የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ጆን ክሪሶስተም “ድሆች ባይኖሩ ኖሮ መዳናችን በአብዛኛው ይበላሻል” ሲል ገልጿል። የእውነተኛው ሕያው አምላክ ምስክሮች እንድንሆን በወንድማማችነት መንገድ ላይ አብረን እንድንሄድ ጌታ ይርዳን ፡፡

20 October 2020, 14:27