ር.ሊ.ጳ ፍራንቸስኮስ በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጳውሎስ አዳራሽ ር.ሊ.ጳ ፍራንቸስኮስ በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጳውሎስ አዳራሽ  

ር.ሊ.ጳ ፍራንቸስኮስ እግዚአብሔር ይሰማናል ፣ ወደ እርሱ በጸሎት መጮኽ ይኖርብናል አሉ!

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ ዘወትር ረቡዕ ዕለት በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጳውሎስ ስድስተኛ አዳራሽ ለሚሰበሰቡ ምዕመናን የጠቅላላ የትምሕርተ ክርስቶስ አስተምህሮ እንደ ሚያደርጉ ይታወቃል። ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ በወቅቱ ያደረጉት የጠቅላላ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ ከዚህ ቀደም በመዝሙረ ዳዊት መጽሐፍ ላይ ትኩረቱን በማደረግ በተከታታይ ያደርጉት ከነበረው አስተምህሮ ቀጣይ ክፍል እንደ ሆነ የተገለጸ ሲሆን የመዝሙረ ዳዊት መጽሐፍ ጸሎት እንዴት መጸለይ እንደ ሚገባን ያስተምረናል ማለታቸው ተገልጿል። በሕይወት ውስጥ ፈተና እና ችግር በሚያጋጥመን ሰዓት እግዚአብሔር የሁላችንም ጸሎት እንደ ሚሰማ በመግለጽ አስተምህሮዋቸውን የጀመሩት ቅዱስነታቸው በዚህም መሰረት ሁልጊዜም ቢሆን በርትተን ልንጸልይ ይገባል ብለዋል።

አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ - ቫቲካን

በጳውሎስ ስድስተኛ አዳራሽ ውስጥ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ ያደረጉት የጠቅላላ አስተምህሮ ከእዚህ ቀደም እንደ ገለጽነው በጸሎት ዙሪያ ላይ ያተኮረ ነው። በዚህ ወቅት ከግምት ውስጥ መግባት ያለበት የመዝሙር ዳዊት መጽሐፍ ነው ፣ “በጸሎት ብቻ የተዋቀረ” የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል “እንዴት መጸለይ እንደሚቻል ማወቅ” በሚሉት ጭብጦች ዙሪያ ላይ ያተኮረ አስተምህሮ ነበር።

በመዝሙረ ዳዊት ውስጥ ሁሉንም የሰዎች ስሜቶችን እናገኛለን - ደስታን ፣ ህመምን ፣ ጥርጣሬዎችን ፣ ተስፋዎችን ፣ ህይወታችንን፣ በቀለማት ያሸበረቁ ሕይወቶችን የመሳሰሉትን ሐሳቦች የሚገኝበት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል እንደ ሆነ በመግለጽ አስተምህሮዋቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው እያንዳንዱ መዝሙር “በሁሉም ሁኔታዎች እና በሁሉም ጊዜያት በእውነት ሊጸልይ የሚችል የመጽሀፍ ቅዱስ ክፍል” መሆኑን ገልጸዋል፣ መዝሙረ ዳዊትን በማንበብ የጸሎትን ቋንቋ እንማራለን በማለት አክለው ገልጸዋል።

ሁሉም ስሜቶቻችን በጸሎት ውስጥ ቦታቸውን ያገኛሉ

በመዝሙረ ዳዊት ውስጥ ስሜታችንን ለመግለጽ ፣ እግዚአብሔርን ለመለመን፣ ለማመስገን፣ እግዚአብሔርን በደስታ እና በመከራ ለመጠየቅ ቃላቱን እናገኛለን በማለት አስተምህሮዋቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው በእነዚህ ጽሑፎች ውስጥ ረቂቅ ሰዎችን አናገኝም፣ነገር ግን በሕይወት ካለው ተሞክሮ የተወሰዱ ጸሎቶችን እናገኛለን ብለዋል።

ወደ እርሱ ለመጸለይ እኛ ማን መሆናችንን ማወቁ በራሱ በቂ ነው፣ እናም ይህንን አይዘንጉ-በደንብ ለመጸለይ፣ ጸሎታችን ተጨባጭ እና አሁናዊ ሊሆን ይገባል በማለት አስተምሕሮዋቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው “ጌታ ሆይ ፣ እኔ እንደዚህ ነኝ” በማለት ማንነታችንን ለእግዚአብሔር በመናገር በእውነተኛ ስሜት ጸሎታችንን ማቅረብ ይኖርብናል ማለታቸው ተገልጿል።

ጌታ ሆይ እስከ መቼ?

ጸሎቶች በውስጣቸው ከያዙት በርካታ ጥያቄዎች መካከል አንዱ “የማያቋርጥ ጩኸት” ይሰማል-ይሄው “እስከ መቼ?” የሚለው ቃል እንደ ሆነ የገለጹት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ “ጌታ ሆይ ፣ እስከ መቼ ድረስ እንዲህ እሰቃያለሁ? ጌታ ሆይ ስማኝ! ”: -“ እስከመቼ? ፣ ጌታ ሆይ… እስከ መቼ? ” በማለት ወደ እግዚአብሔር ጸሎታችንን በመንፈሳዊነት ማቅረብ ይኖርብናል ብለዋል።

አማኙ ግን ለእግዚአብሄር መጮህ ትርጉም እንዳለው ያውቃል ፡፡

እናም ይህ ጩኸት አስፈላጊ ነው፣  ወደ ጸሎት ለመሄድ ስንነሳ የምንሄደው በእግዚአብሔር ፊት ውድ እንደሆንን ስለምናውቅ ነው ወደዚያ ለመጸለይ የምንሄደው በማለት አስተምህሮዋቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው ወደዚህ ጥበብ እንድንሄድ የሚገፋፋን በውስጣችን ያለው የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ነው፣ በእግዚአብሔር ፊት ውድ እንደሆንክ እና ለዚህም ለመጸለይ እንደ ምትሄድ የገለጸልህ የእግዚአብሔር ጸጋ ነው ብለዋል።

ሁለንተናዊ እንባዎች የሉም

የአማኙ ጩኸት በሕመም ፣ በጥላቻ ፣ በጦርነት ፣ በስደት ፣ በመተማመን ፣ በሞት ድራማዎቹ ሁሉ ውስጥ ያስተጋባል፣  መዝሙሮችን የሚያነብ ሁሉ የሰው ጥረት ሁሉ በማይጠቅምበት ቦታ ጣልቃ እንዲገባ እግዚአብሔርን ይጠይቃል በማለት አስተምህሮዋቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው በእግዚአብሔር ፊት ውድ መሆኑን ያውቃል እናም ጸሎት ቀድሞውኑ የመዳን የመጀመሪያ እርምጃ ነው ብለዋል።

በዚህ ዓለም ውስጥ ያለ ማንኛውም ሰው መከራን ይቀበላል-በእግዚአብሔር ቢያምኑም ቢጥሉትም፣ ነገር ግን በመከራ ውስጥ በምንሆንበት ወቅት ወደ እግዚአብሔር ስንጮኸ እርሱ ጸሎታችንን እንደ ሚሰማ በመግልጽ አስተምህሮዋቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው የሚያዳምጠውን የእግዚአብሔር ጆሮ ለመጥለፍ በመጠባበቅ ለእርዳታ መጮኸ ተገቢ እንደ ሆነ ገልጸዋል። ጩኸት ያለ ትርጉም ሊቆይ አይችልም ፡፡ የምንሠቃየው ሥቃይ እንኳን የአጠቃላይ ሕግ የተወሰኑ ጉዳዮች ብቻ ሊሆኑ አይችሉም-እነሱ ሁል ጊዜ “የእኔ” እንባ ናቸው ፣ ከእኔ በፊት ማንም የማያውቀው ችግሬን እግዚአብሔር ስለሚገነዘብ ይቅርታን ያደርግልኛል ብለዋል።

እግዚአብሔር እያንዳንዳችንን በስም ያውቀናል

በእግዚአብሔር ፊት እኛ እንግዶች ወይም ቁጥሮች አይደለንም። እኛ አንድ በአንድ ፣ በስም የምንታወቅ ፊቶች እና ልቦች ነን ሲሉ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳቱ በአስተምህሮዋቸው የተናገሩ ሲሆን  አማኙ የእግዚአብሔር በር ሁል ጊዜ ክፍት መሆኑን ያውቃል ፣ በእርሱ ውስጥ መዳን እንዳለ ይገነዘባል ብለዋል።፡ “ጌታ ያዳምጣል” እናም ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ አፅንዖት ይሰጣሉ-የሚጸልዩ ሰዎች አይታለሉም ፣ የሕይወት ችግሮች ሁል ጊዜ እንደማይፈቱ ያውቃሉ ፣ ግን እነሱ እንደሚደመጡ እርግጠኛ ናቸው ከዚያ በኋላ ሁሉም ነገር የበለጠ የተሻለ እንደ ሚሆን ያምናሉ ካሉ በኋላ ቅዱስነታቸው አስተምህሮዋቸውን አጠናቀዋል።

21 October 2020, 14:51