ር.ሊ.ጳ ፍራንቸስኮስ በጥር 28/2011 ዓ.ም በአቡ ዳቢ መስዋዕተ ቅዳሴ ባሳረጉበት ወቅት

ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ወደ አረብ ባሕረ ሰላጤ አገሮች ባደረጉት የመጀመሪያ ጉብኝታቸው፣ እንደዚሁም የመጀመሪያቸው በሆነው የመስዋዕተ ቅዳሴ ስነ ስርዓት ላይ ለምዕመና በሙሉ ያላቸውን ፍቅር ገልጸዋል። መስዋዕተ ቅድሴውን ለተካፈሉት 180,000 ምዕመናን ዕለቱ የጋራ ጸሎት የቀረበበት የደስታ ዕለት ሆኖ መዋሉ ታውቋል።

ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቺስኮስ ከማቴዎስ ወንጌል ተወስዶ በተነበበው መልዕክት ላይ በመመርኮዝ ባቀረቡት አስተንትኖ ከኢየሱስ ጋር ከሆናችሁ፣ እንደ ደቀ መዛሙርቱ ቃሉንም የምታደምጡ ከሆነ፣ በቃሉም የምትመሩ ከሆነ ብጹዓን ናችሁ ብለዋል። ይህም በክርስትና ሕይወት ውስጥ ማወቅ የቻልነው የመጀመሪያው እውነት ነው ብለዋል። የክርስትና ሕይወት ከሁሉም በላይ የኢየሱስ ክርስቶስ ልጆች መሆናችንን ማወቅ ነው ብለዋል። ይህ ደግሞ ማንም በዚህ ዓለም ላይ ከሕይወታችን ሊነጥቅብን ያማይችለው የደስታችን ምክንያት ነው። ውድ ወንድሞቼ እና እህቶቼ፣ እናንተና ሳገኛችሁ ልነግራችሁ ያፈለኩት ቃል ይህ ነው፣ የተባረካችሁ የሚል ነው ብለዋል።

ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን የተባረካችሁ ናችሁ ሲላቸው፣ እያንዳንዱ ቅዱሳን፣ ቅዱሳን ተብለው የተጠሩበት ምክንያት ለምንድነው ብለን ራሳችንን እንጠይቃለን። ቅዱሳን ተብለው የተጠሩበት ምክንያት በሕዝቦች መካከል እውቅናን ስላተረፉ ወይም ሃብትን ስለ ሰበሰቡ ወይም በሥራቸው ዕውቅናን ስላገኙ ሊመስለን ይችላል። ነገር ግን ለኢየሱስ ክርስቶስ የተቀደሱት ደሆች፣ የተረገጡት፣ የተሰቃዩት እና  የተጨቆኑት ናቸው። ይህን በሚገባ ለመረዳት ኢየሱስ ክርስቶስ እንዴት እንደኖረ መመልከት ያስፈልጋል። ለአንዳንድ ነገሮች ክብርን ለመስጠት ደሃ ነበር፣ ነገር ግን ፍቅርን በማሳየት ሐፍታም ነበር። ብዙ የታመሙ ሰዎችን በማዳን ኣና በመፈወስ ይታወቅ ነበር ነገር ግን የራሱን ሕይወት ከሞት ሊያተርፍ አልቻለም። ሊያገለግል እንጂ ሊገለገል አልመጣም። ትልቅነት የሚገኘው ከመስጠት እንጂ ከመቀበል አይደለም። ፍጹም ትክክል እና ትሑት ሆኖ ሳለ ራሱን ለሕገ ወጥ ፍርድ አቀረበ። በዚህ መንገድ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔርን ፍቅር ወደ ዓለም አምጥቷል በማለት ስብከታቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው ኢየሱስ ክርስቶስን በሙሉ ልብ እንድንከተል የሚያደርገንን የመንፈስ ቅዱስ እገዛን በጸሎት እንጠይቅ በማለት ምዕመናኑን አሳስበዋል።           

Photogallery

ር.ሊ.ጳ ፍራንቸስኮስ በጥር 28/2011 ዓ.ም በአቡ ዳቢ መስዋዕተ ቅዳሴ ባሳረጉበት ወቅት
05 February 2019, 08:55