ር.ሊ.ጳ ፍራንቸስኮስ “ሳትለምነው በፊት ምን እንደ ሚያስፈልግህ በሚያውቀው አባትህ ፊት ሆነህ ጸልይ!”
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራቸስኮስ ዘወትር ረቡዕ እለት በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ወይም በቫቲካን በሚገኘው የጳውሎስ ስድስተኛ የስብሰባ አዳራሻ ለሚሰበሰቡ ምዕመናን፣ መንፈሳዊ ነጋዲያን እና የሀገር ጎብኝዎች በተለያዩ አርእስቶች ላይ ተመርኩዘው የጠቅላላ የትምሕርተ ክርስቶስ አስተምህሮ እንደ ሚያደርጉ ይታወቃል። በዚህ መሰረት በኅዳር 26/2011 ዓ.ም በቫቲካን በሚገኘው የጳውሎስ 6ኛ የስብሰባ አዳራሽ ያደርጉት የጠቅላላ የተምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ “አባታችን ሆይ” በሚለው ጸሎት ላይ መሰረቱን ያደርገ ክፍል አንድ አስተምህሮ እንደ ነበረ መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን “ኢየሱስ ጸሎት መጸለይ እንዲይስተምረን መጠየቅ ይኖርብናል” ማለታቸውን መግለጻችን ይታወሳል።
የዚህ ዝግጅት አቅራቢ መብራቱ ኃ/ጊዮርጊስ-
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ ቀድም ሲል በተከታታይ “አባታችን ሆይ!” በሚለው ጸሎት ዙርያ ዘወትር ረቡዕ እለት ስያደርጉት የነበረውን የጠቅላላ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ የጎርጎሮሳዊያኑን የቀን አቆጣጠር በሚከተሉ የማኅበረሰብ ክፍሎች ዘንድ በቅርቡ ተከብሮ ያለፈውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ ለባለፉት ሁለት ሳምንታት ያህል በእዚህ “አባታችን ሆይ!” በሚለው ጸሎት ዙርያ ስያደርጉት የነበረውን የጠቅላላ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ አቋርጠው እንደ ነበረ የሚታወስ ሲሆን በዛሬው እለት ማለትም በታኅሳስ 24/2011 ዓ.ም አሁንም “አባታችን ሆይ!” በሚለው ጸሎት ዙርያ ባደርጉት የክፍል ሦስት አስተምህሮ ቅዱስነታቸው እንደ ግለጹት “ሳትለምነው በፊት ምን እንደ ምያስፈልግህ በምያውቀው አባትህ ፊት ሆነ ጸልይ” (ማቴ. 6፡6) የእኛ አምላክ የሆነው እግዚኣብሔር እርሱ ከእኛ ምንም አይፈልግም፣ ነገር ግን እርሱ ከእኛ የሚፈልገው አንድ ነገር ቢኖር የእርሱ በጣም ተወዳጅ ልጆቹ የሆንን እኛ በጸሎት ሁልጊዜ ከእርሱ ጋር ለመገናኘት የምያስችለንን የመገናኛ መስመር ሁልጊዜ ክፍት እንድናደርግ ብቻ ነው የሚጠይቀን” ማለታቸውን ለመረዳት ተችሉዋል።
በእለት የተነበቡት ምንባባት
“ስትጸልዩም እንደ ግብዞች አትሁኑ፤ ለሰው ይታዩ ዘንድ በምኩራብና በመንገድ ማዕዘን ቆመው መጸለይን ወዳሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል። አንተ ግን ስትጸልይ፥ ወደ እልፍኝህ ግባ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል” (ማቴ. 6፡5-6)።
ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ በዛሬው እለት ማለትም በታኅሳስ 24/2011 ዓ.ም “አባታችን ሆይ!” በሚለው ጸሎት ዙርያ ያደርጉትን የጠቅላላ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ ሙሉ ይዘት እንደ ሚከተለው ተርጉመነዋል አብራችሁን በመሆን እንድትከታተሉን ከወዲሁ እንጋብዛለን።
የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ እንደ ምን አረፈዳችሁ!
ከዚህ ቀደም “አባታችን ሆይ” በሚለው ጸሎት ዙርያ የጀመርነውን የጠቅላላ የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ በመቀጠል ዛሬ ደግሞ በቅርቡ ባከበርነው የገና በዓል (የጎርጎሮሳዊያኑን የቀን አቆጣጠር በሚከተሉ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን ዘንድ በታኅሳስ 17/2011 ዓ.ም የተከበረውን የገና በዓል ማለታቸው ነው) ምስጢር ብርሃን ታግዘን ቀደም ሲል የጀመርነውን አስተምህሮ እንቀጥላለን።
የማቴዎስ ወንጌል ውስጥ የተጠቀሰው "አባታችን ሆይ" የሚለው ጸሎት በተራራው ላይ በተደርገው ስብከት ማዕከል ውስጥ ቁልፍ የሆነ ቦታ አለው (ማቴ. 6፡9-13)። እስከዚያ ድረስ ሁኔታውን እንመልከት፦ ኢየሱስ በውሃ አጠገብ ወዳለው ኮረብታማ ቦታ ወጣ፣ በዚያም ተቀመጠ። በዙሪያው ለእርሱ እጅግ ቅርብ የነበሩ የእርሱ ደቀ-መዛሙርት ከበውት ነበር፣ ከዚያም በመቀጠል ደግሞ ከተለያዩ ቦታዎች የመጡ የማይታወቁ እጅግ በጣም ብዙ ሰዎች ፊት ለፊቱ ቆመው ነበር። ይህን የመጀመሪያውን "አባታችን ሆይ!" የሚለውን ጸሎት የተቀበሉት/የተማሩት ከተለያዩ አከባቢዎች የተውጣጡ፣ የተለያየ ባሕሪ እና አቋም የነበራቸው የተቀላቀሉ የማኅበርሰብ ክፍል ሰዎች ነበሩ።
ቀደም ሲል እንደ ተጠቀሰው ቦታው (ኢየሱስ “አባታችን ሆይ” የሚለውን ጸሎት ያስተማረበት ኮረብታማ ቦታ ማለት ነው) በጣም ጠቃሚ የሆነ ጥልቅ ትርጉም አለው፣ ምክንያቱም ኢየሱስ “የተራራው ስብከት” (ማቴ. 5፡1-7,27) ተብሎ የሚጠራውን አስተምህሮ ያደረገው በዚህ ስፍራ በመሆኑ የተነሳ ነው። ኢየሱስ በዚያ (በተራራ ላይ ያደርገውን ስብከት) አጠቃላይ የመልእክቱን ይዘት መሠረታዊ ገጽታ ጭብጥ ያቀረባል። በቅድሚያ “የተራራ ላይ” ያደርገውን ስብከት በተዋበ መልኩ እንደ አንድ ተዋኒያን በመሆን በደስታ ያቀርበዋል። ኢየሱስ በእርሱ ዘመን በነበሩ የእርሱ ተከታይ በነበሩ ሰዎች እና በኛም ጭምር ደስተኛ መሆንን አክሎ ይወዳል! እኛ ግን ለእነዚህ ነገሮች ከፍተኛ ግምት ባንሰጥም በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፥ የዋሆች ብፁዓን ናቸው፣ የሚያስተራርቁ ብፁዓን ናቸው፥ ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው
ይህ የመንደርደሪያ ሐሳብ ታሪክዊ የሆኑ እሴቶች በመሻር ቅዱስ ወንጌል በአዲስ መልክ ይገልጻል። አንድ ሕግ መሻር የለበትም፣ ነገር ግን ወደ መጀመርያው ቀድሞ ወደ ነበረው ትርጉሙ የሚመልሰው አዲስ ትርጓሜ ያስፈልገዋል። አንድ ሰው መልካም የሆነ ልብ ካለው፣ ለማፍቀር ዝግጁ ከሆነ እያንዳንዱ የእግዚአብሔር ቃል በመላበስ እስከ መጨረሻው ድረስ መጽናት ይኖርበታል። ፍቅር ምንም ዓይነት ወሰን የለውም ፦አንድ ሰው የትዳር ጓደኛውን፣ የጓደኛውን እና እንዲያውም አንድ ጠላት የሆነውን ሰው እንኳን ሙሉ በሙሉ በአዲስ አመለካከት ሊወድ ይችላል፡ “እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላይ ላለው አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና” (ማቴ 5፡ 44-4)።
“ሁላችሁም በሰማያት ላይ ላለው አባታችሁ ልጆች ናችሁ!” የሚለው ሐረግ በዚህ በተራራውን ላይ በተደርገው ስብከት ውስጥ የሚያንፀባርቅ ታላቁ ምስጢር ነው።
እነዚህ በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ የተጠቀሱት ምዕራፎች (5 እና 6) የስነ-ምግባር ሁኔታዎችን የሚተነትኑ ንግግሮች ይመስላሉ፣ እነዚህን የመሰሉ አስገራሚ የሆኑ የስነ-ምግባር ባሕርያትን የምያነሳሳ ቢመስሉም፣ ነገር ግን ከዚህ ይልቅ እነዚህ ሁሉ ነገረ-መለኮታዊ ይዘት ያላቸው ንግግሮች ናቸው። ክርስቲያን መሆን ማለት ከሌላው የተሻለ ሆኖ ለመገኘት መትጋት ማለት አይደለም፣ ነገር እንደ ሌሎች ሰዎች እርሱም ኃጢኣተኛ እንደ ሆነ ማወቅ ማለት ነው። በቀላሉ ክርስትያን መሆን ማለት በአዲስ መልክ በሚቃጠለው ቁጥቋጦ ፊት ለፊት ራሱን በሚገልጸው አምላክ ፊት በመቆም፣ በማይታወቅ ስሙ አማካይነት የሚታወቀውን ማንነቱን በመግለጽ ልጆቹ ሁሉ “አባት” በሚለው መጠሪያ ስም እንዲጠሩት የሚጠይቃቸውን አምላክ የሚመለከት፣ በእርሱ ኃይል አማካይነት እንዲታደሱ ራሳቸውን የሚያዘጋጁ፣ በእዚህ መልካም ነገሮችን በተጠማው ዓለም ውስጥ የእርሱን መልካምነት የሚያንፀባርቅ የእርሱን መልካም ዜናን በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙ ሰዎች መላካም ዜናውን ማብሰር የሚችል ሰው መሆን ማለት ነው።
ኢየሱስ "የአባታችን ሆይ" የሚለውን ጸሎት ያስተማረው በዚህ መንገድ ነው። እርሱ ይህንን ትምህርት ያስተማረው ከሁለት ቡድኖች ራሱን ባራቀ መልኩ ነው። በመጀመርያ ደረጃ ራሱን አስቀድሞ ከግብዞች ስያርቅ እንመለከታለ፣ ይህንን በተመለከተ ደግሞ እንዲህ ይላል፦ “ስትጸልዩም እንደ ግብዞች አትሁኑ፤ ለሰው ይታዩ ዘንድ በምኩራብና በመንገድ ማዕዘን ቆመው መጸለይን ይወዳሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል” (ማቴ. 6፡5) በማለት ስለ እነርሱ ይገልጻል። አንዳንድ በእግዚኣብሔር የማያምኑ ሰዎች ያለእግዚአብሄር ፀሎት ማድረግ የሚቻል የሚመስላቸው ሰዎች አሉ፣ ይህንንም የሚያደርጉት ከሰዎች ዘንድ አድናቆትን ለማግኘት ፈልገው ነው። በሌላ በኩል ደግሞ የአንድ ክርስቲያን ጸሎት ከአባቱ ጋር በጣም በቅርበት ከሚገናኝበት ከራሱ ሕሊና የተሻለ ሌላ ተጨባጭ እና ታማኝ የሆነ ምስክር የለውም፣ ለዚህም ነው በቅዱስ ወንጌል ውስጥ ኢየሱስ “አንተ ግን ስትጸልይ፥ ወደ እልፍኝህ ግባ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል” (ማቴ. 6፡6) በማለት የተናገረው።
በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ኢየሱስ አረማዊያን ከሚጸልዩት የጸሎት ዓይነት ራሱን ስያርቅ እንመለከታለን፣ ይህንን በተመለከተ ደግሞ እንዲህ ይላል፦ “እናንተ ስትጸልዩ አንደ አረማዊያን ከንቱ ቃላትን በመደጋገም አትለፍልፉ [
የአምላካችንን የእሱን ሞገስ ለማግኘት ለእርሱ መስዋዕት ማቅረብ አስፈላጊ እንዳልሆነ ማሰብ በራሱ ምንኛ ጥሩ ነው! የእኛ አምላክ የሆነው እግዚኣብሔር እርሱ ከእኛ ምንም አይፈልግም፣ ነገር ግን እርሱ ከእኛ የሚፈልገው አንድ ነገር ቢኖር የእርሱ በጣም ተወዳጅ ልጆቹ የሆንን እኛ በጸሎት ሁልጊዜ ከእርሱ ጋር ለመገናኘት የምያስችለንን የመገናኛ መስመር ሁልጊዜ ክፍት እንድናደርግ ብቻ ነው የሚጠይቀን።