ር.ሊ.ጳ ፍራንቸስኮስ፦ “መንፈስ ቅዱስ ልብን እና ክስተቶችን የመቀየር ኃይል አለው”
የግንቦት 12/2010 ዓ.ም “የሰማይ ንግሥት ሆይ ደስ ይበልሽ” ጸሎት
የጎርጎሮሳዊያኑን የቀን አቆጣጠር በሚከተሉ የክርስቲያን ማኅበረሰቦች ዘንድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን በተነሳ በሃምሳኛው ቀን መንፈስ ቅዱስ ለሐዋሪያቱ የላከበት የጴራቂሊጦስ በዓል በትላንትናው እለት ማለትም በግንቦት 12/2010 ዓ.ም ተከብሮ ማለፉ ይታወቃል። ይህ የጴራቂሊጦስ በዓል በግንቦት 12/2010 ዓ.ም. በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ ባዚሊካ በርካታ ቄሳውስት እና ምዕመናን በተገኙበት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ መሪነት ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ተከብሮ ማለፉን ለመረዳት የተቻለ ሲሆን ቅዱስነታቸው በወቅቱ ባሰሙት ስብከት እንደ ገለጹት መንፈስ ቅዱስ ልብን እና ክስተቶችን የመቀየር ኃይል አለው ማለታቸው ተገልጹዋል
የእዚህን አስተንትኖ ሙሉ ይዘት ከእዚህ በታች ያለውን ተጫወት የሚለውን ምልክት በመጫን ማዳመጥ ትችላላችሁ
ክቡራት እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በግንቦት 12/2010 ዓ.ም. በቫቲካን በሚገኘው የቅዱስ ጴጥሮስ ባዚሊካ ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ላይ ያስሙትን ስብከት ሙሉ ይዘት እንደ ሚከተለው ተርጉመነዋል አብራችሁን በመሆን እንድትከታተሉ ከወዲሁ እንጋብዛለን።
20 May 2018, 14:45