ር.ሊ.ጳ ፍራንቸስኮስ፡ “ምስጢረ ጥመቀት የክርስትና ሕይወት መሰረት ነው”
የሚያዝያ 03/2010 ዓ.ም. የጠቅላላ የትምሕርተ ክርስቶስ አሰተምህሮ
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ ዘወትር ረዕቡ እለት በቫቲካን በሚገኘው የጳውሎስ 6ኛ አዳራሽ ወይም ደግሞ እንዳስፈላጊነቱ እና እንደ አየሩ ሁኔታ በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለምሰበሰቡ ምዕመናን እና የሀገር ጎብኝዎች በተለያዩ አርእስቶች ላይ ተመርኩዘው የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ እንደ ሚያደርጉ ይታወቃል። የእዚሁ መርሃ ግብር አንዱ አካል በሆነው ከጥር 7/2010 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ መጋቢት 26/2010 ዓ.ም. ድረስ ዘወትር ረቡዕ እለት በስርዓተ ቅዳሴ ዙሪያ በተከታታይ አድርገውት የነበረው የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ ባለፈው ሳምንት መጠናቀቁ ይታወሳል።
በሚያዝያ 03/2010 ዓ.ም. ረፋዱ ላይ ያደረጉት የትምህርተ ክርስቶስ አስተምህሮ በምስጢረ ጥምቀት ዙሪያ ላይ ያተኮረ እንደ ነበረ የተገጸ ስሆን “ምስጢረ ጥመቀት የክርስትና ሕይውት መሰረት ነው” ማለታቸው ተገልጹዋል።
የእዚህ ዜና አጠናቃሪ--መብራቱ ኃይሌጊዮርጊስ ቫቲካን
ክቡራን እና ክቡራት የዝግጅታችን ታዳሚዎች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በምስጢረ ጥምቀት ዙሪያ ላይ አድርገውት የነበረውን የትምሕርተ ክርስቶስ አስተምህሮ ሙሉ ይዘቱን እንደ ሚከተለው ተርጉመነዋል፣ አብራችሁን በመሆን እንድተከታተሉን ከወዲሁ እናጋብዛለን።
11 April 2018, 15:39