ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮስ፡ “ባልንጄራዎቻችንን መጉዳት እግዚኣብሔርን እንደ ማሳዘን ይቆጠራል”
ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮስ በሚያዝያ 07/2010 ዓ.ም. “የሰማይ ንግሥት ሆይ ደስ ይበልሽ” ከሚለው ጸሎት በፊት በዕለቱ ቅዱስ ወንጌል ላይ ተመርኩዘው ባደርጉት የቅዱስ ወንጌል አስተንትኖ “ ባልንጄራዎቻችንን መጉዳት እግዚኣብሔርን እንደ ማሳዘን ይቆጠራል” ማለታቸው ተገለጸ።
የጎርጎሮሳዊያኑን የቀን አቆጣጠር በሚከተሉ የክርስቲያን ማኅበረሰቦች ዘንድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን የተነሳበት የፋሲካ ወይም የትንሳኤ በዓል ከተከበረ እነሆ ሦስተኛው ሳምንት ላይ እንደ ምንገኝ ይታወቃል። ይህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ የተነሳበት ሦስተኛው የፋሲካ ሳምንት ሰንበት በታላንትናው እለት ማለትም በሚያዝያ 07/2010 ዓ.ም. በቫቲካን በሚገኘው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ መሪነት ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ተከብሮ ማለፉ ታውቁዋል። ቅዱስነታቸው በወቅቱ ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ላይ ባስሙት ስብከት እንደ ገለጹት ባልንጀራችንን መጉዳት እግዚኣብሔርን እንደ ማሳዘን ይቆጠራል ማለታቸው ተገለጸ።
የእዚህ ዜና አቀናባሪ፡ መብራቱ ኃይሌጊዮርጊስ
ክቡራት እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በትላንትናው እለት ማለትም በሚያዝያ 07/2010 ዓ.ም. በቫቲካን በሚገኘው የቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ላይ ያስሙትን ስብከት ሙሉ ይዘት እንደ ሚከተለው ተርጉመነዋል አብራችሁን በመሆን እንድትከታተሉ ከወዲሁ እንጋብዛለን።
15 April 2018, 15:24