ር.ሊ.ጳ ፍራንቸስኮስ “ከኢየሱስ ጋር ጠንካራ የሆነ ግንኙነት የማንፈጥር ከሆንን በተለያዩ አስተሳሰቦች እንወሰዳለን”
የጎርጎሮሳዊያኑን የቀን አቆጣጠር በሚከተሉ የክርስቲያን ማኅበረሰቦች ዘንድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን የተነሳበት የፋሲካ ወይም የትንሳኤ በዓል ከተከበረ እነሆ አራተኛው ሳምንት ላይ እንደ ምንገኝ ይታወቃል። ይህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ የተነሳበት አራተኛው የፋሲካ ሳምንት ሰንበት በዓለማቀፍ ደረጃ 55ኛው ለመነፈሳዊ ጥሪ ጸሎት የሚደርግበት የመላክም እረኛ ሰንበት በመባል የሚታወቅ ሲሆን ይህም የመልካም እረኛ ሰንበት በመባል የሚጠራው ሰንበት በትላንትናው እለት ማለትም በሚያዚያ 14/2010 ዓ.ም. ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በቫቲካን በሚገኘው የቅዱስ ጴጥሮስ ባዚሊካ ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ላይ ለ16 አዳዲስ ካህናት ከሰጡት የማዕረገ ክህነት በመቀጠል እንደ ተለመደው በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለተሰበሰቡ ምዕመናን እና የሀገር ጎብኚዎች በእለቱ ቅዱስ ወንጌል ላይ አስተንትኖ ማድረጋቸው የተገለጸ ሲሆን በወቅቱ ባሰሙት አስተንትኖ “ከኢየሱስ ግራ ጠንካራ የሆነ ግንኙነት የማንፈጥር ከሆንን የተለያዩ መንገዶችን የሚጠቁሙን አስተሳሰቦች ሰልባ እንሆናልን” ማለታቸው ተገልጹዋል።
ክቡራት እና ክቡራት የዝግጅቶቻችን ተከታታዮች ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ በትላንትናው እለት ማለትም በሚያዝያ 14/2010 ዓ.ም. በቫቲካን በሚገኘው የቅዱስ ጴጥሮስ ባዚሊካ ካሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ በመቀጠል በቅዱስ ጴጥሮስ አደባባይ ለተሰበሰቡ ምዕማናን እን የሀገር ጎብኚዎች ያደርጉትን የወንጌል ላይ አስተንትኖ ሙሉ ይዘት እንደ ሚከተለው ተርጉመነዋል አብራችሁን በመሆን እንድተከታተሉ ከወዲሁ እንጋብዛለን።