ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ በሰኔ 12/2010 ዓ.ም  በቫቲካን በሚገኘው በቅድስት ማርታ የጸሎት ቤት ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ በሰኔ 12/2010 ዓ.ም በቫቲካን በሚገኘው በቅድስት ማርታ የጸሎት ቤት   (© VATICANMEDIA S.S. Francesco - Messa Domus Sanctae Marthae 11-01-2018)

ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮስ፡ ክርስቲያን ለጠላቱ ይጸልያል፣ ጠላቱንም ይወዳል

“ክርስቲያን ለጠላቱ ይጸልያል፣ ጠላቱንም ይወዳል”

ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ “ክርስቲያን ለጠላቱ ይጸልያል፣ ጠላቱንም ይወዳል” ማለታቸው ተገለጸ።

ቅዱስነታቸው ይህንን ቀደም ሲል የተጠቀሰውን የተናገሩት በዛሬው እለት ማለትም በሰኔ 12/2010 ዓ.ም በቅድስት ማርታ የጸሎት ቤት ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ላይ ባሰሙት ስብከት እንደ ነበረ ለመረዳት የተቻለ ሲሆን “ጠላቶቻችሁን ውደዱ ለሚያሳድዱዋችሁ ሰውች ጸልዩ” የሚለው የጽሐፍ ቅዱስ ቃል እግዚኣብሔር ቅዱስ እንደ ሆነ ሁሉ እኛም ቅዱስ እንድንሆን የሚረዳን በመሆኑ የተነሳ ክርስቲያኖች ይህንን ሊከተሉ የገባል ብለዋል።

የዚህ ዜና አጠናቃሪ መብራቱ ኃይለጊዮርጊስ ቫቲካን

በእለቱ ከማቴዎስ ወንጌል ከምዕራፍ 5፡43 ተወስዶ በተነበበው የቅዱስ ወንጌል ክፍል ላይ ተመርኩዘው እኛን ሊያጠፉን ለሚፈልጉ ጠላቶቻችን በሙሉ ይቅርታን ማድረግ እና ጸሎት መጸለይ እንደ ሚገባ በመግለጽ ስብከታቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው ሁሉን አቀፍ የሆነ ፍቅር ያለውን የሰማያዊ አባታችን ጥሪ ተከትለን ለሰው ልጆች ከፍተኛ ተግዳሮት የሆነውን ጠላትን የመውደድ መንፈስ ማዳበር እንደ ሚገብ የጠቀሱት ቅዱስነታቸው እግዚኣብሔር ይህንን ጠላቶቻችንን መውደድ የሚያስችለን ጸጋ ይሰጠን ዘንድ ልንጠይቀው የገባል ብለዋል።

ይቅር ለመባል በቅድሚያ ይቅር እንበል

 በእየዕለቱ አባታችን ሆይ የሚለውን ጸሎት በምንጸልይበት ወቅት “እኛን የበደሉንን ይቅር እንደ ምንል በደላችንን ይቀር በለን” የሚለውን ጸሎት እንደ ምንጸልይ በማስታወስ ስብከታቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው በእዚህም ምክንያት ጠላቶቻችንን ይቅር ማለት እንደ ሚገባ የገለጹት ቅዱስነታቸው ምንም እንኳን ይህ ቀላል የሚባል ነገር ባይሆንም ቅሉ እኛ ይቅር እንደ ምንል ሁሉ ሌሎችም ይቅርታ እንዲያደርጉልን ልንጠይቅ የገባል ብለዋል።  በተመሳሳይ መልኩም ለሌሎች ሰዎች በተለይም በእኛ ላይ ብዙን ጊዜ ችግር ለሚያደርሱብን፣ ለሚጠሉን እና ወደ ፈተና ውስጥ ለሚከቱን ሰዎች ሳይቀር ምንም እንኳን ከባድ የሚባል ነገር ቢሆንም መጸለይ እንደ ሚገባ የገለጹት ቅዱስነታቸው ይህም የአንድ ክርስቲያን የመገለጫ ባሕሪይ ሆኖ ሊቀጥል እንደ ሚገባ ቅዱስነታቸው ጨምረው ገልጸዋል። ይህንን ሐሳባቸውን በሚገባ ለማስረጽ በማሰብ ቅዱስነታቸው የሚከተለውን ብለዋል. . .

“እኔን ለማጥፋት ለሚፈልጉ ሰዎች፣ ለጠላቶቼ እግዚኣብሔር ይባርካቸው ዘንድ መጸለይ፡ ይህ ነገር በእውነት ለማረዳት በጣም ከባድ የሆነ ነገር ነው። ባለፈው ምዕተ አመት በራሻ በነበሩ ክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመውን ግፍ እናስታውሳለን፣ ክርስቲያኖች በመሆናቸው ብቻ በብርድ እንዲሞቱ በጣም ቀዝቅዛ ወደ ሆነው ወደ ሳይቤሪያ ይላኩ ነበር፣ ታዲያ እነዚህ ክርስቲያኖች በብርድ እንዲሞቱ ወደ እዚያ ለላካቸው የመግሥት ባለስልጣን መጸለይ ይኖርባቸዋል ወይ? ነገር ግን እንዴት? ብዙዎቹ ይህንን አድርገዋል፣ ብዙዎቹም ጸልየዋል። ኦሽዊትስ እና ሌሎች የማጎሪያ ካምፖች እናስብ፡ እነርሱ ለእዚህ እኔ ንጹህ ዘር ነኝ ብሎ ይመካ እና ሰዎችን ያለምንም ርኅራኄ ይገድል ለነበረው አባገንን ለነበረ ሰው እግዚኣብሔር ይባርከው ዘንድ ጸልየው ነበር። ብዙዎቹም በእዚህ መልኩ ጸልየው ነበር።”

ከኢየሱስ እና ሰማዕታት ከነበራቸው ስነ-አመክንዮ እንማር

ኢየሱስ በመስቀል ላይ በነበረበት ወቅት በመጨረሻ ሰዓት ላይ እርሱን ስያሰቃዩ የነበሩ ሰዎችን “ጌታ ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው” በማለት ያደርገውን የማጠቃለያ ጸሎት ሁኔታውን መረዳት በጣም አስቸጋሪ እንደ ሆነ የገለጹት ቅዱስነታቸው ኢየሱስ ግን ይህንን ያቅርታ አድርጎላቸው ነበር ብለዋል። በተመሳሳይ መልኩም ሰመዕቱ እስጢፋኖስ የኢየሱስን ፈለገ በመከተል በድንጋይ ይወግሩት ለነበሩ ሰዎች ይቅርታ እንዳደረገላቸው የገለጹት ቅዱስነታቸው ይህንን በተመለከተ ደግሞ የሚከተለውን ብለዋል. . .

“ይህ ነገር እኛ በጣም ብዙን ጊዜ ትናንሽ ለሚባሉ ነገሮች ሳይቀር ይቅርታ ማድረግ ለሚከብደን ለእኛ ምን ያህል ርቀት ይኖረው ይሆን? እግዚኣብሔር ከእኛ የሚጠብቀው እና በምሳሌነት በተግባር እንዳሳየን ሁሉ እኛን ልያጠፉን የሚፈልጉ ሰዎችን ይቅር ልንል ይገባል። በቤተሰብ ውስጥም ቢሆን ይህ ጉዳይ በጣም ቀላል የሚባል ጉዳይ አይደለም፣ አንዳንዴ ከሆኑ ክርክሮች በኃላ ይቅር መባባል ይከብዳል፣ ቀላል የሆነ ነገር አይድለም። ልጅ አባቱን ይቅርታ መጠየቅ በጣም ይከብደው ይሆናል። ነገር ግን በተለይም ደግሞ ልያጠፉን ሊገሉን የሚፈልጉ ሰዎችን ይቅር ማለት ብቻ ሳይሆን እግዚኣብሔር ይባርካቸው እና ይጠብቃቸው ዘንድ ለእነርሱ መጸለይ! እናም ከእዚያም አልፎ ተርፎ እነርሱን መውደድ። ይህንን በይበልጥ እንድንረዳ የሚረዳን የኢየሱስ ቃል ብቻ ነው። እኔ ከእዚህ በላይ በመሄድ ይህንን ላብርራ አልችልምና።”

በእዚህም ምክንያት ይህንን ታላቅ የክርስቲያኖች ምስጢር የሆነውን ነገር ለመረዳት እንችል ዘንድ ጸጋውን እንዲሰጠን ልንጸልይ ይግባል በማለት ስብከታቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው ሁሉንም ነገር በእኩልነት በክፉዎች ላይ ይሁን በደጎች ላይ የሚያዘንበው ሰማያዊ አባታችን ቅዱስ እንደ ሆነ እኛም ቅዱሱ እንሆን ዘንድ ጸጋውን እንዲሰጠን ልንለምነው ይገባል ብለዋል።

ቅዱስነታቸው በስብከታቸው ማጠቃለያ ላይ እንደ ገለጹት ተስፋ አደርጋለሁ እኛ እያንዳንዳችን ጠላቶች ይኑሩናል ብዬ አስባለሁ፣ ስለጠላቶቻችን ማሰብ ጥሩ የሆነ ስሜት እንዲሰማን ሊያደርገን እንደ ሚችል የጠቀሱት ቅዱስነታቸው ይህንን በተመለከተ ደግሞ የሚከተለውን ብለዋል . . .

“ዛሬ ጠላቶቻችንን ማሰብ መልካም ይሆናል-ተስፋ አደርጋለሁ እኛ እያንዳንዳችን ጠላቶች አሉን- በእኛ ላይ ክፉ ነገር የፈጸሙብን፣ ወይም ክፉ ነገር ለመፈጸ የሰቡ ሰዎች ሊኖሩ ይችሉ ይሆናል። በእዚህ ረገድ አንድ ማፊያ የሆነ ሰው ሲጸልይ “ታገኛታለህ፣ ዋጋ ያስከፍልሃል! የሚለው ነው። በእዚህ ረገድ አንድ ክርስቲያን ሲጸልይ ግን “ጌታ ሆይ በረከትህን ስጠው፣ እንድወደው አስተምረኝ” የሚለው ነው። አስቲ አንድ ጠላት የሆነ ሰው እናስብ። ሁላችንም ይነስም ይብዛም አንድ ጠላት አለን። እርሱን እናስብ። ስለእርሱ እንጸልይ። ጌታ ጠላታችንን እንድወድ ጸጋውን እንዲሰጠን ልንለምነው የገባል።”

 

19 June 2018, 16:18
ሁሉንም ያንብቡ >