ር.ሊ.ጳ. ፍራንቸስኮ ..መንፈስ ቅድስ የስብከተ ወንጌል ዋነኛው አጋዥ ነው
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ ዘወትር ጥዋት በቫቲካን በሚገኘው የቅድስት ማርታ የጸሎት ቤት ለሚሰበሰቡ ቀሳውስት፣ ደናግልና እና ምዕመናን መስዋዕተ ቅዳሴን እንደ ሚያሳርጉ የሚታወቅ ሲሆን በእዚህ መሰረት በሰኔ 04/2010 ዓ.ም በአውሮፓዊያኑን የቀን አቆጣጠር የላቲን የስርዓተ አምልኮ የቀን አቆጣጠር ደንብ መሰረት የቅዱስ ባርናባስ አመታዊ በዓል በተከበረበት ወቅት ባሳረጉት መስዋዕተ ቅዳሴ ላይ ባሰሙት ስብከት እንደ ገለጹት በማንኛውም ስብከተ ወንጌልን በማሰራጨት ሂደት ውስጥ መንፈስ ቅዱስ “ተዋናይ” መሆኑን ቅዱስነታቸው ገለጸዋል።
የእዚህ ዜና አቀናባሪ መብራቱ ኃይሌጊዮርጊስ ቫቲካን
ቅድሱ ወንጌልን የማብሰር ሂደት ከሌሎች የመገናኛ ዓይነቶች ጋር ተመሳሳይ የሆነ ጉዳይ አለምሆኑን በመግለጽ ስብከታቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው ቅዱስ ወንጌልን የማስበር ሂደት በመንፈስ ቅዱስ ድጋፍ የሚከናወን በመሆኑ የተነሳ ልብን የመቀየር ኃይል አለው ብለዋል። አንዳንድ ጊዜ በጣም ምርጥ የሚባሉ ሐዋሪያዊ ተግባራትን የማከናወኛ እቅዶች ቢኖሩም እንኳን እነዚህ ምርጥ የተባሉ ሐዋሪያዊ እቅዶች በራሳቸው ልብን የመለወጥ ኃይል ወይም ብቃት እንደ ሌላቸው በመግለጽ ስብከታቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው እነዚህ እቅዶች በራሳቸው ወድ ግብ እንድናመራ የሚያደጉን ናቸው እንጂ በራሳቸው ወደ ግብ መስመር መውሰጃ መሳሪያዎች ግን አይደሉም ብለዋል።
ቅዱስነታቸው ይህንን አሳባቸውን ለማጠናከር በማሰብ የሚከተለውን ብለዋል . . .
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮ አገልግሎት ሁለተኛው ቅዱስ ወንጌልን የማብሰር ሂደት ገጽታ አድርገው የሚመለከቱ ሲሆን እንዲያውም ቅዱስነታቸው ይህንን በተመለከተ "አንድ ሰው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አገልግሎትን ወይም ስኬትን የሚፈልግ ከሆነ ይህ ሰው ቅዱስ ወንጌልን ምንም እንደማያውቅ የሚያሳይ ምልክት ነው፣ የሚያዝ ሰው በራሱ የሚያገለግል ሰው ሊሆን የገባዋል” የሚል ከፍተኛ አቋም እንዳላቸው ይታወቃል።
ቅዱስነታቸው ይህንን በተመለከተ ደግሞ የሚከተለውን ብለዋል. . .
ወንጌል በነፃ የሚሰጥ ነው
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ የስብከተ ወንጌል አገልግሎት በነጻ የሚሰጥ አገልግሎት መሆኑ ደግሞ የወንጌላዊነት ሦስተኛው የመገለጫ ገጽታ እንደ ሆነ የጠቀሱ ሲሆን ምክንያቱም ማንም ቢሆን በራሱ ብርታ ታግዞ የዳነ ሰው ባለመኖሩ የተነሳ ነው፣ በመሆኑ የተነሳ እንደ ሆነ ገለጸው ቅዱስ ወንጌል “ በነጻ የተቀበላችሁትንም በነጻ ስጡ” በማለት እንደ ሚናገር ቅዱስነታቸው አስታውሰዋል።
ይህንን በተመለከተ ደግሞ ቅዱስነታቸው የሚከተለውን ብለዋል. . .