ብጹዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ መንግሥተአብ ለሰላም የአንድ ወር የጸሎት ጊዜ አወጁ
ብጹዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ መንግሥተአብ ለሰላም የአንድ ወር የጸሎት ጊዜ አወጁ
በቅርቡ በኢትዮጲያ እና በኤርትራ መንግሥታት መከካል የነበረው ፍጥጫ ተወግዶ በሁለቱም ሀገራት መካከል የሰላም አየር መንፈስ ከጀመረ እነሆ በርካታ ቀናት ተቆጥረዋል። በሁለቱም ሀገራት የሚገኙ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ምዕመናን በሁሉቱ እህት ሀገራት ውስጥ ሰላም ይሰፍን ዘንድ በተደጋጋሚ ሲማጸኑ እና ጸሎት ሲያደርጉ እንደ ቆዩ ይታወሳል። እነሆ የሰላም አለቃ በሆነው በእግዚኣብሔር ፈቃድ፣ በምዕምናን ጸሎት እና በጎድ ፈቃድ ባላቸው ሰዎች መልካም ፈቃድ እንዲሁም በሁለቱ ሀገራት መንንግሥታት በጎ ፈቃድ በአሁኑ ወቅት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ልዩነት እየተወገደ የሰላም ንፋስ መንፈስ ጀምሩዋል፣ ግንኙነቱ በተለያዩ በማሕበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ እና በፖሌቲካዊ ዘርፎች እየተሻሻለ መምጣቱ ይታወቃል።
በቅርቡ በኤርትራ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን የአስመራ ሊቀ ጳጳስ የሆኑት ብፅዕ አቡነ መንግሥተአብ ተስፋማሪያም በኢትዮጲያ እና በኤርትራ መንግሥታት መካከል የተጀመረው ሰላማዊ ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል በማሰብ በኤትራ እና በመላው ዓለም የሚገኙ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ምዕመናን እና በጎ ፈቃድ ያላቸው ሰዎች ሁሉ ከሐምሌ 1 እስከ ነሐሴ 6/2010 ዓ.ም ድረስ ለአንድ ወር ያህል ማለት ነው ጸሎት እንዲደረግ ማወጃቸውን ከስፍራው ለቫቲካን ሬዲዮ ከደርሰው መረጃ ለመረዳት ተችሉዋል።
በኤርትራ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን የአስመራ ሊቀ ጳጳስ የሆኑት ብፅዕ አቡነ መንግሥተአብ ተስፋማሪያም ለእዚህ ለአንድ ወር ያህል ለሚቆየው የጸሎት ዝግጅት አስተንትኖ ይሆን ዘንድ የመረጡት መልእክት የተወሰደው ከካቶሊክ ቤተክርስቲያን ትምሕርተ ክርስቶስ ከቁጥር 2304 ላይ የተወሰደውን እንደ ሚከተለው እናቀርብላችኃለን።
የሰላም መንፈስ በኤርትራ እና በኢትዮጲያ መካከል ተጠናክሮ እንድቀጥል በማሰብ በኤርትራ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን የአስመራ ሊቀ ጳጳስ የሆኑት ብፅዕ አቡነ መንግሥተአብ ተስፋማሪያም ያስተላለፉትን መልእክት ሙሉ ይዘቱን እንደ ሚከተለው አሰንዳተናዋል።
በኤርትራ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን
የአስመራ ሊቀ ጳጳስ
ብፅዕ አቡነ መንግሥተአብ ተስፋማሪያም